ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ የደመወዝ ጭማሪ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን የገንዘብ ሚኒስትሩ ገለጹ|salary |zena |ethiopiainsider
Вставка
- Опубліковано 9 жов 2024
- ዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ የደመወዝ ጭማሪ፤ ከትላንት በስቲያ በተካሄደው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ መጽደቁን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። የደመወዝ ጭማሪው 92 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት መጠየቁንም የገንዘብ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት፤ ከሁለት ወራት በፊት መተግበር የጀመረውን የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያዎች አስመልክቶ በትላንትናው ዕለት ለመንግስት ቅርበት ላለው ፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው። ባለፈው ሐምሌ ወር መጨረሻ ይፋ የተደረገውን ይህን የፖሊሲ ማሻሻያ ተከትሎ፤ ኢትዮጵያ “በገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርዓት” ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች።
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም አካል የሆነውን የእዚህን የፖሊሲ ለውጥ አፈጻጸም የሚገመግም ስብሰባ በትላንትናው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ተካሄዶ ነበር። በስብሰባው የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ “ፖሊሲው በስኬታማ አፈጻጸም ላይ መሆኑን ያለፉት ሁለት ወራት አሳይተዋል” ሲሉ በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያው ተፈጻሚ በሆነባቸው ወራት “የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬ ከባቢን መመልከት ችለናል” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የገቢ ግባችንም የተቀመጠለትን ግብ በመምታት በታለመለት መንገድ ላይ ይገኛል” ሲሉ የአፈጻጸም ግምገማ ውጤቱን አብራርተዋል። በትላንቱ ስብሰባ ላይ የተሳተፉት እና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አህመድ በበኩላቸው፤ የፖሊሲ ማሻሻያው “በጎላ መልኩ ማህበራዊ ጫና እንዳያስከትል” በወጣው እቅድ መሰረት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ለፋና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴 ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
yes thankyu
Thank you
Ok
እረ የጡረተኞች ችግርና ሰቆቃ እየባሠበት ነው መንግስት አንድ ይበላቸው እኛም ድምፅ እንሁናቸው
በትክክል ለጡረተኞች በሚገባ ችግር ውስጥ ነው ያሉት እኮ
no change will come
Ahiya ahiyawn new yemiakew, fandiya gimatam.
እውነት አይመስለንም
ከመች ነው እዲሡ የሚጀመረው