Розмір відео: 1280 X 720853 X 480640 X 360
Показувати елементи керування програвачем
Автоматичне відтворення
Автоповтор
Best of best poem bertalegni wondime fetari yebarkih
jegna yeJegna lij. nullijn. the best poam. well done bro.
how he is a good poet የኔ ውድ ወንድም በርታልኝ ዘመኖችህ ሁሉ የተባረኩ ይሁኑ
👌👌👌ከዓመታት በፊት እንዲህ ስል ስንኝ ቋጥሬ ነበር።የዚህ ግጥም መነሻም አቶ ተፈሪ አለሙ በአንድ ወቅት "ቋሚ ሰው ተናገር" በሚል ርዕስ ላቀረቡት ግጥም የተሰጠ ምላሽ ነው።በወቅቱ በማዳምጥው ግጥምና በምስል ተደገፎ ይቀርብ በነበረው ማስረጃ ከሚገባው በላይ ልቤ ለሰማዕታቱ ክፉኛ ደምቷል። እንደዚህ አይነት ስሜት ውስጥ ስሆን ደግሞ መጫር እወዳለሁ።ከአክብሮት ጋር።**************ምን ቋሚ ሰው አለ★★★★★★★ገበየሁ አባቴ፣ አዎን ብለህ ነበርቋሚ ሰው፣ ተናገርጀብዴን፣ ለአለም አብስርክንዴ እንደሰበረ፣ የሞሶሌንን ቅጥርበአጭር እንደቀጨ፣ የእብሪተኛን ሚስጥርበደስታ እንደሰጠሁ፣ አጥንትና ደሜን ለኢትዮጵያ ክብር።ገበየሁ አባቴ፣ በአውነት ነው የምልህ እንዳንተ ፍላጎት፣ ልክ እንደ ምኞትህምንም ቋሚ የለበአባላጌ ጋራ፣ በአድዋ የዋለጀብድህን ሊደግመው፣ በአፅምህ የማለአደራ ያልከውን፣ ታሪክህን ሚጠብቅመች ቋሚ ተገኝቶ፣ ቃልህን አድምጦ፣ በገድልህ ሚደምቅግን በተቃራኒው፣ አጥንትና ደምክን በአንድ ላይ ቀይጦሌላ ደም ሚያስከፍል፣ ቃላቶችን መርጦበረቀቀ ዘዴ፣ አገር ቆርጦ ሽጦደግሞ በላዩ ላይ፣ ወደብ የሚመርቅለምን ባይ ጠያቂን፣ ወገን ሚያሸማቀቅበምስጋና ፋንታ፣ ከርቸሌ ሚያማቅቅገድልህን አጥቁሮ፣ ህገመንግስት ሚያረቅአገር በቁም አስሮ፣ በጎሳና በጎጥ፣ በሴራ ሚራቀቅበስርቆት በአፈናው፣ በአድሎው ሚመፃደቅከጣና በለስ ትልም፣ ከዕራይ የሚያራርቅእርኩስ መንፈስ በቅሎ፣ የደምህን ወጤት፣ ባንዲራን የሚል ጨርቅእንኳን በክብር ሞትክ፣ ይህንን ጉድ ሳታይየሀገርክን መቸብቸብ፣ የታሪክህን መጉደፍ፣ በአብራክህ ክፋይ።ገበየሁ አባቴ፣ ምን ቋሚ ሰው አለ እንዳንተ አባላጌ፣ በአድዋ የዋለገድልህን ሊደግመው፣ በስምህ የማለበሚያሳዝን መልኩ፣ ቴዎድሮስ ዮሃንስ፣ ሚኒሊክ እመየንዘራይና እና አብዲሳ፣ አቢቹ በላይንብዙ ሰማዕታት፣ እንዳንተ እንቁዎችንነፍጠኛ በማለት፣ ሚያጎድፍ ገድላችሁንየሀገር መጥፎ ህመም፣ ከፋፋይ ታቅፈንቋሚ ሰው የት ይገኝ፣ ዘካሪ ታሪክንጠባብ ትምክተኛ፣ ፊውዳል ሳይባል፣ ሚያነሳ ስምህን።ገበየሁ አባቴ፣ ምን ቋሚ ሰው አለእንዳንተ አባላጌ፣ በማይጨው የዋለሂድ ንገር ያልከውን፣ ሚመሰክር ገድልህንአደራ ያልከውን፣ የጠበቀ ቃልክንበእውነት ነው ምልህዛሬ ላይ አላይም፣ የማለ በስምህ።በሚያሳፍር መልኩ፣ ጥላቻን የሚሰብክለዜጋው ማይራራ፣ ለባህድ ሚብረከረክየጎጥ ዛር አጓርቶ፣ ግዑዝ ወንበር ሚያመልክበብሄር ከበሮ፣ በክልል ጥሩንባናላችንን ሚያዞር፣ በነጋ በጠባአፅምህን ወሮታል፣ ከፋሽሽት ሚስጥሮበጊዚያዊ ስልጣን፣ በባህድ ዶላር ሰክሮወገን በቃኝ እሰኪል፣ አንገት ደፍቶ ኑሮበክብር እስኪቀብርህ፣ ቋሚ ዘራፍ እስኪል፣ በዋይተህ ተማሮ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።መታሰቢያነቱ: በህይወት ላሉ እንዲሁም ለአርበኛ ገበየሁ ጎራው፣ ለዮፍታሔ ንጉሤ እና ለሌሎችም አፅማቸው በታሪክ ጉዶች ከተቀበረበት ተቆፍሮ ወጥቶ ለአመታት በአልባሌ ሁኔታ ለተንከራተተ የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ሰማዕታት።★★★★★★★★★ዛሬ ደግሞ እንዲህ ስንኝ ቋጨሁ።**************************ትውልድ ይታየኛል★************ወጣት፣ ይታየኛል ቄሮ፣ ይታየኛልፋኖ ይታየኛልኮበሌ፣ ይታየኛልዘርማ አለሁ፣ ይለኛል።በአንድ ለአምስት ሴራ፣ ሲመሽ የባተተለትህነግ ያልሸሸ፣ አልሞ ያልሳተጉግሰኛ ለመሆን፣ ነጭ ፈረስ የሻተትውልድ ይታየኛል፣ የተዛባ ታሪክ፣ የተተረከለትለቅድመ አያቶቹ፣ አድዋ ለቀሩትበቁጨት የሚበግን፣ እውነቱን ደርሶበትአዎ! በሃሳብ ይነጉዳልበሲቃ፣ ይዋጣልለሰሜን ዕዝ ጀግና፣ ለማይካድራ ንፁሃን፣ ከልቡ ይቆጫልደማቸውን ሊያብስ፣ ገድላቸውን ሊደግም፣ ቃል ኪዳን ይገባል።አዎ! ቄሮ ይታየኛልፋኖ ይታየኛልኮበሌ ይታየኛልዘርማ ይጠራኛልነብሮ አለሁ ይለኛል።ማንነቱ የገባው፣ ወጣት ትኩስ ሃይልጥቁር ሰውን ሚያዜም፣ አንዲት ኢትዮጵያ የሚልከጠበኩት በላይ፣ ትዉልድ ይታየኛልፍቅር ያሸንፋል፣ ኢትዮጵያ ቤቴ ሚልብረት ሳያነሳ፣ ሴራ እያከሸፈ የተቀዳጀ ድልጥበት ተጠይፎ፣ ዜግነትን ሚሰብክለእኩይ ለጉግማንጉግ፣ የማይበረከክበኢትዮጵያዊነቱ ፀንቶ፣ አይዞህ ወንድሜ ሚልልክ እንደ አንደበቱ፣ አነጣጥሮ ሚጥልየአሎሌን መርዝ ነቅሎ፣ በርግብ የታጀበ ዘንባባ ሚተክልጎጠኝነት ይወደም፣ አንድ ኢትዮጵያ የሚል።***-************----******ክብር ለኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ቅድመ አያቶቻችን፣ ፍትህ በጥቂት ጉግማንጉጎች እኩይ ደባና ሴራ በግፍ ለተሰዉ ዕንቁ የሐገር መከላከያ ሰራዊት ሰማዕታት፣ ከቅያቸው ለሚፈናቀሉ ለሚታገቱ ከትምህርት ገበታቸው ለሚጉላሉ በግፍ ለሚገደሉ በባዶ ስድስት ማሰቃያ እስርቤቶችና ጭቃኔ በተሞላበት ሁኔታ ለተገደሉና ያላግባብ በእስር ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች።አንድ ኢትዮጵያ፣ አንድ ሕዝብ!!!ዔልፋዖስ ኒቐሥ
መልኬ ብቻ ብዬ ራሴን ከምቆልል ያለኝን አቅም ልጠቀም እስኪ ሰብስክራይብ በማድረግ ልግስናችሁን ግለፁልኝ 🙏🏾💚💛❤
👌👌👌 "ወጥመድን ለወፎች በከንቱ የሚያጠምዱእግሮቻቸው ወደ ክፋት ይሮጣሉከጎዳናቸውም እግርህን ፈቀቅ አድርግ ደም ለማፍስፈሰስ ይፈጥናሉና" ታላቁ መፅሃፍ ★★★★★★" ነፃ አውጭዎቻችሁ እኛ ነን እያሉ ነፃነቱን ከሚነፍጉት ሞራለ ቢሶች፣ ነፃነቱን በተስፋ የሚጠብቅ ዜጋ ከቁራ መልክተኞችም ከራሱም በፍፁም ነፃ አይወጣም"። ከእኔምክንያቱም ወደዚች ምድር ሲመጣ በቅድመ አያቶቹ የተከሰከሰ አጥንትና የፈሰሰ ክቡር ደም ነፃነቱ ከትውልድ ትውልድ ሲወራረድ እንደመጣ ሊዘክሩለትና ሊያስተምሩት በማይሹ የጋራ ታሪክ የለንም ባዮች የባህድ የሚስጢር ኪስ የእናት ጡት ነካሾች በለጋ አዕምሮው ያልበር ማንነትና ጥላቻ በተስፋየ የኮኽን ብዕር በረቀቀና በተቀነባበረ መልኩ ሲግቱት ነፃ ሆኖ የመፈጠሩ ስብዕና በዕቡ ጉግማንጉጎች እኩይ አስተምሮ እንደማይታደለው አስረግጦ ባለመናገሩ ነው።ይኸንንም አይቶ እንዳላየ የሚያይ፣ እስኪያልፍ ያለፋል እያለ፣ የሚተክዝን ዜጋ፣ ትግስትና አርቆ አስተዋይነቱን፣ እንደ ፍርሃት በመቁጠር፣ ጥበት፣ የበታችነት ስሜትና ስብዕና የተጠናዎታቸው ፣ ራዕያቸው ከሃገር ልዑዓላዊነት፣ ከወገን ደህንነትና፣ በሳላም ውሎ ማደር ይልቅ፣ በጎጥ ዙሪያ፣ የልዮነት ሹርባ እየጎነጎኑ፣ ድርና ማግ ሆኖ ሚኖር ህዝብን፣ በማይቆም የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መክተት፣ የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ሰላምና ብልፅግና ማይሹ ባህዳንን፣ እኩይ ተልዕኮ ማስፈፀም፣ ባፈናቀሉት ወገን ስም፣ ምፅዋት መሰበሰብና፣ የህገወጥ መሳሪያ ደላላ ሆኖ፣ የስልጣን ዘመንን ማራዘምና፣ ቀፈትን መሙላት ነው።ለዚህም ተልዕኳቸው ደግም፣ ለምን እንዴት ስለምን፣ ወዴት ለማን ብለው የማይጠይቁ፣ ሩጠው ያልጠገቡ፣ የነገ ሃገር ተረካቢዎችን ህይወት፣ እስቀማስቀጠፍ እኩይ ሴራ ያሴራሉ። "**ፍቅር እስክንገዛ★-★----★እንደ ዕንቁ እያየቸኝ፣ በእናትነት አይኗ ተመስጣ ሀገሬእንደ ልብህ ቦርቅ፣ እንዳሻህ ኑርባት በቅድስቷ ምድሬብላ ስትመክረኝ፣ ከጎና አስቀምጣ፣ ፍቅር እየመገበች በእጆቿ ለፀጉሬመች ህልሜ እውን ቢሆን፣ ብመረቅ ተምሬበክልል ሸንሽኖን፣ የአንችው እኩይ ፍሬብየ መልስ እንዳልሰጥ፣ ለእምየ ለፍቅሬበደሌን ስሰማ፣ ልቧ እንዳይሰበር፣ ሃዘኗ እንዳይበዛከወንድም ተፋልሜ፣ ክብሯን እያስጠበኩ፣ ለአብራክ ቅጥረኛ፣ ለሴራው ልገዛእሱ ጎጥ አቅሮት፣ እኔም በፀሎቴ፣ ፍቅር እስክንገዛ።በየአቅጣጫው ለሚፈናቀሉ፣ በየትምህርት ተቋሙ ለሚሞቱ፣ የብሄር ፖለቲካው ሰለባዎችና ለኢትዮ ኤርትራ ተጎጅዎች።**👌 👌 👌 👌ከአያት የተላከ ስንኝ****************በብሔር ብሔረሰቡ ስም፣ ላም አለኝ በሰማይ ቀፋዮችነፃ ባልወጣ ነፃ አውጭ፣ ማንነትሽ የተገፈፈችደም በተጠሙ ጎጠኞች፣ በእነ እኩይ ታሪክ ፈታዮችዜግነት ያጣህ ወዳጀ፣ የሆንክ አጅ ተወርችመፅናኛ ጉልበት ይሁንህ፣ ተቀበል ከአያት ስንኞች★★★★★★★★★የሀገር ትርጉም ሚስጥሩን፣ ገና ጠልቀህ ሳታውቀውኢትዮጰያዊ ነኝ አትበለኝ፣ አፍህን በእኔ ስም አታሟሸውበሰማዕታት ደም አጥንት፣ በተገኘው ነፃነትአትደንፋበት አታቅራራ፣ አንተ ከምኑም የለህበትየነፃነት ተምሳሌ ነኝ፣ ቅኝ ተገዝቸ አላውቅምብለህ አትፎክር በጉራ፣ በፍፁም ነፃ አይደለህምፋሽስት ወራሪን አርበድብደው፣ ነፃ ቢያቆዩ ኢትዮጵያንምን ተረፋቸው ሰማዕታት፣ ቅድመ አያት ምዕምናንበስማቸው ተመጳድቀህ፣ በገድላቸው ተኩራርተህመቸ ታሪክ ስትደግም፣ ባንዲራህን ስጠብቅ ታየህ።እናም ልጀ ወዳጀ ሆይ፣ በአንድ ወቅት ቅኝ ገዥዎች ቢወሩኝም፣የነፃነት ውጤት ነኝ፣ ባርነትን አላውቅምብለህ አትደንፋ በጉራ፣ በፍፁም ነፃ አልወጣህምእስኪ ቆም ብለህ አስተውል፣ ጠያቂ ይሁን አይዕምሮትውልድ ለዘመናዊ ባርነት፣ በነፃ አውጭ ነኝ ባይ፣ በደላላ ተሸጋግሮወገን ክብር ተነፍጎት፣ ከቆሻሻ ጋር ተወርውሮበሰበብ በአሰባቡ፣ ዜጋ ባዶ ስድስት ተጠፍሮ ጤንነትህ ተቃውሶ፣ ጠኔ አንጀትህ ተቀብሮማንነትህ ተገፎ፣ ስብዕናህ በረንዳ አድሮልሳንህ በአፈሙዝ፣ በአንድ ላምስት ተቸንክሮየህግ ያለህም ስትል፣ ስታሰማ እሮሮለህይወትህ ዋስትና፣ ትውልድ ጎጥህ ተቆጥሮከአንተ በዕውቀት ሚያንሰው፣ በዘመድ አዝማድ ተቀጥሮየመጨረሻ እጣ ፈንታህ፣ ስደት እና እንጉርጉሮያውም የዘንድሮውስ ባርነት፣ በራስህ የአብራክህ ክፋይቀየ ጎሳህን ተገን አርጎ፣ ከእድር ከቀየህ ፈንቃይየእናት ጡት ነካሽ ሆኖ፣ አንዲት ሀገርህን ከፋፋይ።እናም ልጀ ወዳጀ ሆይ፣በፍጱም፣ ቀኝ ተገዝቸ አላውቅምየነፃነት ውጤት ነኝ፣ በባርነት አላለፍኩምብለህ አትደንፋ በጉራ፣ በፍፀጱም ነፃ አይደለህምበእከከኝ ልከክልህ፣ ጊዚያዊ ጥቅም ተተብትበህእውነታው ውስጥህ ታምቆ፣ ውሸት ከሆነ አንደበትህውስጥህ በፍርሀት ሲርድ፣ ከንፈር መምጠጥ ከሆነ ምርጫህዜጋ በግፍ ሲገደል፣ ያለ ሐጢያቱ ሲማቅቅእንዴት ስለምን ብለህ፣ ያንተን የሱን መብት ሳጠይቅታዲያ በምን ሂሳብ ነው፣ እኔ ነፃ ነኝ ምትለኝበሙሰኛ ዳኛ አቃቢ፣ ያለ በደሌ ወንጅለህኝበውሸት አስመስክረህ፣ በቁመናየ ቀብረህኝ በፅናቴ ክፋት ቋጥረህ፣ ከእርምጃየ ገተህኝመስጊድ ደብር ተደግፈህ፣ቁራን ዳዊት አነብንበህ፣ፍትህን ከልክለህኝታዲያ በምን ሂሳብ ነው፣ ነፃ ሰው ነኝ ምትለኝ።እናም እውነት እውነት እልሀለሁ፣ ልጀ ወዳጀ ሆይያውም የባሪያ ባሪያ፣ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይግዑዝ አካልህ ከርሱን እንጅ፣ ስዕብናውን የማያይወገንህ ግፍ በዝቶበት፣ እራሱን በእሳት ሲያቃጥልየተቀደሰ ንፁህ ህይወት፣ ሲጣል በዱር በገደልውሃ በአንድ ኮዳ የጠጣ፣ የሐገር መከታ ሰራዊት፣ በባልጀራው ሲገደልየነፃ ሰው ተምሳሌት ሆነህ፣ከጠገበው ጋር ጮቤ ሳትረግጥ፣ ጊዜ ላነሰው ሳትነጠፍከስርቆቱ ከግድያው፣ በይሉኝታ ሳትለጠፍየተከፋን ልብ ሳታደማ፣ የለመለመን ሳታነጠፍእውነትን እሬት ሳትቀባ፣ ውሸትን ሸልመህ ሳታቅፍለምን ማለት ስትጀምርለዜጎች ነፃነት ክብር፣ያላድሎ ስትከራከርለሀገር ለወገን ዕልውና፣ በፅዕኑ ስትፉለምጎጠኝነትን አሽቀንጥረህ፣ ስለ አንድ ኢትዮጵያ ስታልምብሄር ቀለም የግል ጥቅም፣ ከምናብህ ሲፀዳእውነትን ምርኩዝ አርገህ፣ ስትወጣ ከጔዳሙሉ ሰው የምትባል፣ ቃልኪዳኑን የማይከዳእሄኔ ነው በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ፣ ቅኝ ተገዝቸ አላውቅምብለህ መመፃደቅ ያለብህ፣ በስብዕናህ ስትኮራ፣ ውስጥህን ሲሰማው ሰላምጥላህን ሳትፈራ፣ ሳትኖር በቅዠት አለምየተቦተለከልህን ሳይሆን፣ የራስህን ራዕይ ስታልምእሄኔ ነው በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ፣ ቅኝ ተገዝቸ አላውቅምየነፃነት ውጤት ነኝ፣ በባርነት አላለፍኩምብለህ መመፃደቅ ያለብህ፣ ውስጥህን ሲሰማው ሰላም።********************ክብር ለቅድመ አያቶቻችንና መከላከያ ሰራዊታችን፣ ፍትህ በጥቂት ጉግማንጉጎች እኩይ ደባና ሴራ በግፍ ለተሰዉ ዕንቁ የሐገር መከላከያ ሰራዊት ሰማዕታት፣ ከቅያቸው ለሚፈናቀሉ ለሚታገቱ ከትምህርት ገበታቸው ለሚጉላሉ በግፍ ለሚገደሉ በባዶ ስድስት ማሰቃያ እስርቤቶችና ጭቃኔ በተሞላበት ሁኔታ ለተገደሉና በእስር ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች።★★አንድ ኢትዮጵያ፣ አንድ ሕዝብ!!!★ዔልፋዖስ ኒቐሥ
አቦ ብዕርህ አዪንጠፍ
ephye berta jegna neh
Best of best poem bertalegni wondime fetari yebarkih
jegna yeJegna lij. nullijn. the best poam. well done bro.
how he is a good poet የኔ ውድ ወንድም በርታልኝ ዘመኖችህ ሁሉ የተባረኩ ይሁኑ
👌👌👌
ከዓመታት በፊት እንዲህ ስል ስንኝ ቋጥሬ ነበር።
የዚህ ግጥም መነሻም አቶ ተፈሪ አለሙ በአንድ ወቅት "ቋሚ ሰው ተናገር" በሚል ርዕስ ላቀረቡት ግጥም የተሰጠ ምላሽ ነው።
በወቅቱ በማዳምጥው ግጥምና በምስል ተደገፎ ይቀርብ በነበረው ማስረጃ ከሚገባው በላይ ልቤ ለሰማዕታቱ ክፉኛ ደምቷል። እንደዚህ አይነት ስሜት ውስጥ ስሆን ደግሞ መጫር እወዳለሁ።
ከአክብሮት ጋር።
**************
ምን ቋሚ ሰው አለ
★★★★★★★
ገበየሁ አባቴ፣ አዎን ብለህ ነበር
ቋሚ ሰው፣ ተናገር
ጀብዴን፣ ለአለም አብስር
ክንዴ እንደሰበረ፣ የሞሶሌንን ቅጥር
በአጭር እንደቀጨ፣ የእብሪተኛን ሚስጥር
በደስታ እንደሰጠሁ፣ አጥንትና ደሜን ለኢትዮጵያ ክብር።
ገበየሁ አባቴ፣ በአውነት ነው የምልህ
እንዳንተ ፍላጎት፣ ልክ እንደ ምኞትህ
ምንም ቋሚ የለ
በአባላጌ ጋራ፣ በአድዋ የዋለ
ጀብድህን ሊደግመው፣ በአፅምህ የማለ
አደራ ያልከውን፣ ታሪክህን ሚጠብቅ
መች ቋሚ ተገኝቶ፣ ቃልህን አድምጦ፣ በገድልህ ሚደምቅ
ግን በተቃራኒው፣ አጥንትና ደምክን በአንድ ላይ ቀይጦ
ሌላ ደም ሚያስከፍል፣ ቃላቶችን መርጦ
በረቀቀ ዘዴ፣ አገር ቆርጦ ሽጦ
ደግሞ በላዩ ላይ፣ ወደብ የሚመርቅ
ለምን ባይ ጠያቂን፣ ወገን ሚያሸማቀቅ
በምስጋና ፋንታ፣ ከርቸሌ ሚያማቅቅ
ገድልህን አጥቁሮ፣ ህገመንግስት ሚያረቅ
አገር በቁም አስሮ፣ በጎሳና በጎጥ፣ በሴራ ሚራቀቅ
በስርቆት በአፈናው፣ በአድሎው ሚመፃደቅ
ከጣና በለስ ትልም፣ ከዕራይ የሚያራርቅ
እርኩስ መንፈስ በቅሎ፣ የደምህን ወጤት፣ ባንዲራን የሚል ጨርቅ
እንኳን በክብር ሞትክ፣ ይህንን ጉድ ሳታይ
የሀገርክን መቸብቸብ፣ የታሪክህን መጉደፍ፣ በአብራክህ ክፋይ።
ገበየሁ አባቴ፣ ምን ቋሚ ሰው አለ
እንዳንተ አባላጌ፣ በአድዋ የዋለ
ገድልህን ሊደግመው፣ በስምህ የማለ
በሚያሳዝን መልኩ፣ ቴዎድሮስ ዮሃንስ፣ ሚኒሊክ እመየን
ዘራይና እና አብዲሳ፣ አቢቹ በላይን
ብዙ ሰማዕታት፣ እንዳንተ እንቁዎችን
ነፍጠኛ በማለት፣ ሚያጎድፍ ገድላችሁን
የሀገር መጥፎ ህመም፣ ከፋፋይ ታቅፈን
ቋሚ ሰው የት ይገኝ፣ ዘካሪ ታሪክን
ጠባብ ትምክተኛ፣ ፊውዳል ሳይባል፣ ሚያነሳ ስምህን።
ገበየሁ አባቴ፣ ምን ቋሚ ሰው አለ
እንዳንተ አባላጌ፣ በማይጨው የዋለ
ሂድ ንገር ያልከውን፣ ሚመሰክር ገድልህን
አደራ ያልከውን፣ የጠበቀ ቃልክን
በእውነት ነው ምልህ
ዛሬ ላይ አላይም፣ የማለ በስምህ።
በሚያሳፍር መልኩ፣ ጥላቻን የሚሰብክ
ለዜጋው ማይራራ፣ ለባህድ ሚብረከረክ
የጎጥ ዛር አጓርቶ፣ ግዑዝ ወንበር ሚያመልክ
በብሄር ከበሮ፣ በክልል ጥሩንባ
ናላችንን ሚያዞር፣ በነጋ በጠባ
አፅምህን ወሮታል፣ ከፋሽሽት ሚስጥሮ
በጊዚያዊ ስልጣን፣ በባህድ ዶላር ሰክሮ
ወገን በቃኝ እሰኪል፣ አንገት ደፍቶ ኑሮ
በክብር እስኪቀብርህ፣ ቋሚ ዘራፍ እስኪል፣ በዋይተህ ተማሮ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
መታሰቢያነቱ: በህይወት ላሉ እንዲሁም ለአርበኛ ገበየሁ ጎራው፣ ለዮፍታሔ ንጉሤ እና ለሌሎችም አፅማቸው በታሪክ ጉዶች ከተቀበረበት ተቆፍሮ ወጥቶ ለአመታት በአልባሌ ሁኔታ ለተንከራተተ የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ሰማዕታት።
★★★★★★★★★
ዛሬ ደግሞ እንዲህ ስንኝ ቋጨሁ።
**************************
ትውልድ ይታየኛል
★************
ወጣት፣ ይታየኛል
ቄሮ፣ ይታየኛል
ፋኖ ይታየኛል
ኮበሌ፣ ይታየኛል
ዘርማ አለሁ፣ ይለኛል።
በአንድ ለአምስት ሴራ፣ ሲመሽ የባተተ
ለትህነግ ያልሸሸ፣ አልሞ ያልሳተ
ጉግሰኛ ለመሆን፣ ነጭ ፈረስ የሻተ
ትውልድ ይታየኛል፣ የተዛባ ታሪክ፣ የተተረከለት
ለቅድመ አያቶቹ፣ አድዋ ለቀሩት
በቁጨት የሚበግን፣ እውነቱን ደርሶበት
አዎ! በሃሳብ ይነጉዳል
በሲቃ፣ ይዋጣል
ለሰሜን ዕዝ ጀግና፣ ለማይካድራ ንፁሃን፣ ከልቡ ይቆጫል
ደማቸውን ሊያብስ፣ ገድላቸውን ሊደግም፣ ቃል ኪዳን ይገባል።
አዎ! ቄሮ ይታየኛል
ፋኖ ይታየኛል
ኮበሌ ይታየኛል
ዘርማ ይጠራኛል
ነብሮ አለሁ ይለኛል።
ማንነቱ የገባው፣ ወጣት ትኩስ ሃይል
ጥቁር ሰውን ሚያዜም፣ አንዲት ኢትዮጵያ የሚል
ከጠበኩት በላይ፣ ትዉልድ ይታየኛል
ፍቅር ያሸንፋል፣ ኢትዮጵያ ቤቴ ሚል
ብረት ሳያነሳ፣ ሴራ እያከሸፈ የተቀዳጀ ድል
ጥበት ተጠይፎ፣ ዜግነትን ሚሰብክ
ለእኩይ ለጉግማንጉግ፣ የማይበረከክ
በኢትዮጵያዊነቱ ፀንቶ፣ አይዞህ ወንድሜ ሚል
ልክ እንደ አንደበቱ፣ አነጣጥሮ ሚጥል
የአሎሌን መርዝ ነቅሎ፣ በርግብ የታጀበ ዘንባባ ሚተክል
ጎጠኝነት ይወደም፣ አንድ ኢትዮጵያ የሚል።
***-************----******
ክብር ለኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ቅድመ አያቶቻችን፣ ፍትህ በጥቂት ጉግማንጉጎች እኩይ ደባና ሴራ በግፍ ለተሰዉ ዕንቁ የሐገር መከላከያ ሰራዊት ሰማዕታት፣ ከቅያቸው ለሚፈናቀሉ ለሚታገቱ ከትምህርት ገበታቸው ለሚጉላሉ በግፍ ለሚገደሉ በባዶ ስድስት ማሰቃያ እስርቤቶችና ጭቃኔ በተሞላበት ሁኔታ ለተገደሉና ያላግባብ በእስር ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች።
አንድ ኢትዮጵያ፣ አንድ ሕዝብ!!!
ዔልፋዖስ ኒቐሥ
መልኬ ብቻ ብዬ ራሴን ከምቆልል ያለኝን አቅም ልጠቀም እስኪ ሰብስክራይብ በማድረግ ልግስናችሁን ግለፁልኝ 🙏🏾💚💛❤
👌👌👌
"ወጥመድን ለወፎች በከንቱ የሚያጠምዱ
እግሮቻቸው ወደ ክፋት ይሮጣሉ
ከጎዳናቸውም እግርህን ፈቀቅ አድርግ ደም ለማፍስፈሰስ ይፈጥናሉና" ታላቁ መፅሃፍ
★★★★★★
" ነፃ አውጭዎቻችሁ እኛ ነን እያሉ ነፃነቱን ከሚነፍጉት ሞራለ ቢሶች፣ ነፃነቱን በተስፋ የሚጠብቅ ዜጋ ከቁራ መልክተኞችም ከራሱም በፍፁም ነፃ አይወጣም"። ከእኔ
ምክንያቱም ወደዚች ምድር ሲመጣ በቅድመ አያቶቹ የተከሰከሰ አጥንትና የፈሰሰ ክቡር ደም ነፃነቱ ከትውልድ ትውልድ ሲወራረድ እንደመጣ ሊዘክሩለትና ሊያስተምሩት በማይሹ የጋራ ታሪክ የለንም ባዮች የባህድ የሚስጢር ኪስ የእናት ጡት ነካሾች በለጋ አዕምሮው ያልበር ማንነትና ጥላቻ በተስፋየ የኮኽን ብዕር በረቀቀና በተቀነባበረ መልኩ ሲግቱት ነፃ ሆኖ የመፈጠሩ ስብዕና በዕቡ ጉግማንጉጎች እኩይ አስተምሮ እንደማይታደለው አስረግጦ ባለመናገሩ ነው።
ይኸንንም አይቶ እንዳላየ የሚያይ፣ እስኪያልፍ ያለፋል እያለ፣ የሚተክዝን ዜጋ፣ ትግስትና አርቆ አስተዋይነቱን፣ እንደ ፍርሃት በመቁጠር፣ ጥበት፣ የበታችነት ስሜትና ስብዕና የተጠናዎታቸው ፣ ራዕያቸው ከሃገር ልዑዓላዊነት፣ ከወገን ደህንነትና፣ በሳላም ውሎ ማደር ይልቅ፣ በጎጥ ዙሪያ፣ የልዮነት ሹርባ እየጎነጎኑ፣ ድርና ማግ ሆኖ ሚኖር ህዝብን፣ በማይቆም የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መክተት፣ የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ሰላምና ብልፅግና ማይሹ ባህዳንን፣ እኩይ ተልዕኮ ማስፈፀም፣ ባፈናቀሉት ወገን ስም፣ ምፅዋት መሰበሰብና፣ የህገወጥ መሳሪያ ደላላ ሆኖ፣ የስልጣን ዘመንን ማራዘምና፣ ቀፈትን መሙላት ነው።
ለዚህም ተልዕኳቸው ደግም፣ ለምን እንዴት ስለምን፣ ወዴት ለማን ብለው የማይጠይቁ፣ ሩጠው ያልጠገቡ፣ የነገ ሃገር ተረካቢዎችን ህይወት፣ እስቀማስቀጠፍ እኩይ ሴራ ያሴራሉ። "
**
ፍቅር እስክንገዛ
★-★----★
እንደ ዕንቁ እያየቸኝ፣ በእናትነት አይኗ ተመስጣ ሀገሬ
እንደ ልብህ ቦርቅ፣ እንዳሻህ ኑርባት በቅድስቷ ምድሬ
ብላ ስትመክረኝ፣ ከጎና አስቀምጣ፣ ፍቅር እየመገበች በእጆቿ ለፀጉሬ
መች ህልሜ እውን ቢሆን፣ ብመረቅ ተምሬ
በክልል ሸንሽኖን፣ የአንችው እኩይ ፍሬ
ብየ መልስ እንዳልሰጥ፣ ለእምየ ለፍቅሬ
በደሌን ስሰማ፣ ልቧ እንዳይሰበር፣ ሃዘኗ እንዳይበዛ
ከወንድም ተፋልሜ፣ ክብሯን እያስጠበኩ፣ ለአብራክ ቅጥረኛ፣ ለሴራው ልገዛ
እሱ ጎጥ አቅሮት፣ እኔም በፀሎቴ፣ ፍቅር እስክንገዛ።
በየአቅጣጫው ለሚፈናቀሉ፣ በየትምህርት ተቋሙ ለሚሞቱ፣ የብሄር ፖለቲካው ሰለባዎችና ለኢትዮ ኤርትራ ተጎጅዎች።
**
👌 👌 👌 👌
ከአያት የተላከ ስንኝ
****************
በብሔር ብሔረሰቡ ስም፣ ላም አለኝ በሰማይ ቀፋዮች
ነፃ ባልወጣ ነፃ አውጭ፣ ማንነትሽ የተገፈፈች
ደም በተጠሙ ጎጠኞች፣ በእነ እኩይ ታሪክ ፈታዮች
ዜግነት ያጣህ ወዳጀ፣ የሆንክ አጅ ተወርች
መፅናኛ ጉልበት ይሁንህ፣ ተቀበል ከአያት ስንኞች
★★★★★★★★★
የሀገር ትርጉም ሚስጥሩን፣ ገና ጠልቀህ ሳታውቀው
ኢትዮጰያዊ ነኝ አትበለኝ፣ አፍህን በእኔ ስም አታሟሸው
በሰማዕታት ደም አጥንት፣ በተገኘው ነፃነት
አትደንፋበት አታቅራራ፣ አንተ ከምኑም የለህበት
የነፃነት ተምሳሌ ነኝ፣ ቅኝ ተገዝቸ አላውቅም
ብለህ አትፎክር በጉራ፣ በፍፁም ነፃ አይደለህም
ፋሽስት ወራሪን አርበድብደው፣ ነፃ ቢያቆዩ ኢትዮጵያን
ምን ተረፋቸው ሰማዕታት፣ ቅድመ አያት ምዕምናን
በስማቸው ተመጳድቀህ፣ በገድላቸው ተኩራርተህ
መቸ ታሪክ ስትደግም፣ ባንዲራህን ስጠብቅ ታየህ።
እናም ልጀ ወዳጀ ሆይ፣
በአንድ ወቅት ቅኝ ገዥዎች ቢወሩኝም፣
የነፃነት ውጤት ነኝ፣ ባርነትን አላውቅም
ብለህ አትደንፋ በጉራ፣ በፍፁም ነፃ አልወጣህም
እስኪ ቆም ብለህ አስተውል፣ ጠያቂ ይሁን አይዕምሮ
ትውልድ ለዘመናዊ ባርነት፣ በነፃ አውጭ ነኝ ባይ፣ በደላላ ተሸጋግሮ
ወገን ክብር ተነፍጎት፣ ከቆሻሻ ጋር ተወርውሮ
በሰበብ በአሰባቡ፣ ዜጋ ባዶ ስድስት ተጠፍሮ
ጤንነትህ ተቃውሶ፣ ጠኔ አንጀትህ ተቀብሮ
ማንነትህ ተገፎ፣ ስብዕናህ በረንዳ አድሮ
ልሳንህ በአፈሙዝ፣ በአንድ ላምስት ተቸንክሮ
የህግ ያለህም ስትል፣ ስታሰማ እሮሮ
ለህይወትህ ዋስትና፣ ትውልድ ጎጥህ ተቆጥሮ
ከአንተ በዕውቀት ሚያንሰው፣ በዘመድ አዝማድ ተቀጥሮ
የመጨረሻ እጣ ፈንታህ፣ ስደት እና እንጉርጉሮ
ያውም የዘንድሮውስ ባርነት፣ በራስህ የአብራክህ ክፋይ
ቀየ ጎሳህን ተገን አርጎ፣ ከእድር ከቀየህ ፈንቃይ
የእናት ጡት ነካሽ ሆኖ፣ አንዲት ሀገርህን ከፋፋይ።
እናም ልጀ ወዳጀ ሆይ፣
በፍጱም፣ ቀኝ ተገዝቸ አላውቅም
የነፃነት ውጤት ነኝ፣ በባርነት አላለፍኩም
ብለህ አትደንፋ በጉራ፣ በፍፀጱም ነፃ አይደለህም
በእከከኝ ልከክልህ፣ ጊዚያዊ ጥቅም ተተብትበህ
እውነታው ውስጥህ ታምቆ፣ ውሸት ከሆነ አንደበትህ
ውስጥህ በፍርሀት ሲርድ፣ ከንፈር መምጠጥ ከሆነ ምርጫህ
ዜጋ በግፍ ሲገደል፣ ያለ ሐጢያቱ ሲማቅቅ
እንዴት ስለምን ብለህ፣ ያንተን የሱን መብት ሳጠይቅ
ታዲያ በምን ሂሳብ ነው፣ እኔ ነፃ ነኝ ምትለኝ
በሙሰኛ ዳኛ አቃቢ፣ ያለ በደሌ ወንጅለህኝ
በውሸት አስመስክረህ፣ በቁመናየ ቀብረህኝ በፅናቴ ክፋት ቋጥረህ፣ ከእርምጃየ ገተህኝ
መስጊድ ደብር ተደግፈህ፣
ቁራን ዳዊት አነብንበህ፣
ፍትህን ከልክለህኝ
ታዲያ በምን ሂሳብ ነው፣ ነፃ ሰው ነኝ ምትለኝ።
እናም እውነት እውነት እልሀለሁ፣ ልጀ ወዳጀ ሆይ
ያውም የባሪያ ባሪያ፣ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይ
ግዑዝ አካልህ ከርሱን እንጅ፣ ስዕብናውን የማያይ
ወገንህ ግፍ በዝቶበት፣ እራሱን በእሳት ሲያቃጥል
የተቀደሰ ንፁህ ህይወት፣ ሲጣል በዱር በገደል
ውሃ በአንድ ኮዳ የጠጣ፣ የሐገር መከታ ሰራዊት፣ በባልጀራው ሲገደል
የነፃ ሰው ተምሳሌት ሆነህ፣
ከጠገበው ጋር ጮቤ ሳትረግጥ፣ ጊዜ ላነሰው ሳትነጠፍ
ከስርቆቱ ከግድያው፣ በይሉኝታ ሳትለጠፍ
የተከፋን ልብ ሳታደማ፣ የለመለመን ሳታነጠፍ
እውነትን እሬት ሳትቀባ፣ ውሸትን ሸልመህ ሳታቅፍ
ለምን ማለት ስትጀምር
ለዜጎች ነፃነት ክብር፣
ያላድሎ ስትከራከር
ለሀገር ለወገን ዕልውና፣ በፅዕኑ ስትፉለም
ጎጠኝነትን አሽቀንጥረህ፣ ስለ አንድ ኢትዮጵያ ስታልም
ብሄር ቀለም የግል ጥቅም፣ ከምናብህ ሲፀዳ
እውነትን ምርኩዝ አርገህ፣ ስትወጣ ከጔዳ
ሙሉ ሰው የምትባል፣ ቃልኪዳኑን የማይከዳ
እሄኔ ነው በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ፣ ቅኝ ተገዝቸ አላውቅም
ብለህ መመፃደቅ ያለብህ፣ በስብዕናህ ስትኮራ፣ ውስጥህን ሲሰማው ሰላም
ጥላህን ሳትፈራ፣ ሳትኖር በቅዠት አለም
የተቦተለከልህን ሳይሆን፣ የራስህን ራዕይ ስታልም
እሄኔ ነው በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ፣ ቅኝ ተገዝቸ አላውቅም
የነፃነት ውጤት ነኝ፣ በባርነት አላለፍኩም
ብለህ መመፃደቅ ያለብህ፣ ውስጥህን ሲሰማው ሰላም።
********************
ክብር ለቅድመ አያቶቻችንና መከላከያ ሰራዊታችን፣ ፍትህ በጥቂት ጉግማንጉጎች እኩይ ደባና ሴራ በግፍ ለተሰዉ ዕንቁ የሐገር መከላከያ ሰራዊት ሰማዕታት፣ ከቅያቸው ለሚፈናቀሉ ለሚታገቱ ከትምህርት ገበታቸው ለሚጉላሉ በግፍ ለሚገደሉ በባዶ ስድስት ማሰቃያ እስርቤቶችና ጭቃኔ በተሞላበት ሁኔታ ለተገደሉና በእስር ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች።
★★
አንድ ኢትዮጵያ፣ አንድ ሕዝብ!!!
★
ዔልፋዖስ ኒቐሥ
አቦ ብዕርህ አዪንጠፍ
ephye berta jegna neh