መጽሐፈ ዕዝራ ከምዕራፍ 6 እስከ ምዕራፍ 10
Вставка
- Опубліковано 10 лют 2025
- 🧡 መጽሐፈ ዕዝራ ክፍል 2 🧡
🧡ምዕራፍ 6፦ ዳርዮስ በባቢሎን ቤተ መዛግብት ያሉ መጻሕፍት እንዲመረመሩ ማዘዙ
ቤተ መቅደስ ተሠርቶ መጠናቀቁ
🧡ምዕራፍ 7፦ ዕዝራ ለእስራኤል ሥርዓትንና ፍርድን ያስተምር ዘንድ ልቡን አዘጋጅቶ እንደነበር
-ንጉሥ አርተሰስታ (አርጤክስስ) የእግዚአብሔርን ቤት በሚሠሩ አገልጋዮች ግብርና ቀረጥ እንዳይጣልባቸው ማዘዙ
🧡ምዕራፍ 8፦ ከባቢሎን ስለወጡት አይሁድ መነገሩ
-እስራኤል ጾምን እንዳወጁ፣ እግዚአብሔርን እንደለመኑና እርሱም እንደሰማቸው
🧡ምዕራፍ 9፦ ዕዝራ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ጋር ተጋብተው ባየ ጊዜ እንዳዘነና እንደጸለየ
🧡ምዕራፍ 10፦ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ሚስቶቻቸው (ባሎቻቸው) እንደተለዩ
🧡 የዕለቱ ጥያቄዎች 🧡
፩. ሁለተኛው ቤተ መቅደስ ተሠርቶ የተጠናቀቀው መቼ ነው?
ሀ. በንጉሡ ቂሮስ መንግሥት በመጀመሪያው ዓመት
ለ. በንጉሡ ዳርዮስ መንግሥት በስድስተኛው ዓመት
ሐ. በንጉሡ ቂሮስ መንግሥት በስድስተኛው ዓመት
መ. በንጉሡ ዳርዮስ በመጀመሪያው ዓመት
፪. በመጽሐፈ ዕዝራ መሠረት የእግዚአብሔርን ቤት በሚሠሩ ሰዎች ግብርና ቀረጥ እንዳይጣል ያደረገው ንጉሥ ማን ነው?
ሀ. ንጉሥ አርጤክስስ
ለ. ንጉሥ አርተሰስታ
ሐ. ንጉሥ ሰናክሬም
መ. ሀ እና ለ