መጽሐፈ ዕዝራ ከምዕራፍ 6 እስከ ምዕራፍ 10

Поділитися
Вставка
  • Опубліковано 10 лют 2025
  • 🧡 መጽሐፈ ዕዝራ ክፍል 2 🧡
    🧡ምዕራፍ 6፦ ዳርዮስ በባቢሎን ቤተ መዛግብት ያሉ መጻሕፍት እንዲመረመሩ ማዘዙ
    ቤተ መቅደስ ተሠርቶ መጠናቀቁ
    🧡ምዕራፍ 7፦ ዕዝራ ለእስራኤል ሥርዓትንና ፍርድን ያስተምር ዘንድ ልቡን አዘጋጅቶ እንደነበር
    -ንጉሥ አርተሰስታ (አርጤክስስ) የእግዚአብሔርን ቤት በሚሠሩ አገልጋዮች ግብርና ቀረጥ እንዳይጣልባቸው ማዘዙ
    🧡ምዕራፍ 8፦ ከባቢሎን ስለወጡት አይሁድ መነገሩ
    -እስራኤል ጾምን እንዳወጁ፣ እግዚአብሔርን እንደለመኑና እርሱም እንደሰማቸው
    🧡ምዕራፍ 9፦ ዕዝራ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ጋር ተጋብተው ባየ ጊዜ እንዳዘነና እንደጸለየ
    🧡ምዕራፍ 10፦ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ሚስቶቻቸው (ባሎቻቸው) እንደተለዩ
    🧡 የዕለቱ ጥያቄዎች 🧡
    ፩. ሁለተኛው ቤተ መቅደስ ተሠርቶ የተጠናቀቀው መቼ ነው?
    ሀ. በንጉሡ ቂሮስ መንግሥት በመጀመሪያው ዓመት
    ለ. በንጉሡ ዳርዮስ መንግሥት በስድስተኛው ዓመት
    ሐ. በንጉሡ ቂሮስ መንግሥት በስድስተኛው ዓመት
    መ. በንጉሡ ዳርዮስ በመጀመሪያው ዓመት
    ፪. በመጽሐፈ ዕዝራ መሠረት የእግዚአብሔርን ቤት በሚሠሩ ሰዎች ግብርና ቀረጥ እንዳይጣል ያደረገው ንጉሥ ማን ነው?
    ሀ. ንጉሥ አርጤክስስ
    ለ. ንጉሥ አርተሰስታ
    ሐ. ንጉሥ ሰናክሬም
    መ. ሀ እና ለ

КОМЕНТАРІ •