አንደኛ መቃብያን ከምዕራፍ 21 እስከ ምዕራፍ 26
Вставка
- Опубліковано 5 лют 2025
- 💜 መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ክፍል 5 💜
💜ምዕራፍ ፳፩፡-
-ዳዊት በእግዚአብሔር በመታመኑ ከሳኦልና ከሌሎችም ጠላቶቹ እጅ እንደዳነ መነገሩ
-ድል መንሣት ከእግዚአብሔር እንደሆነ መገለጡ
-እግዚአብሔር ሕጉን በማይጠብቅ ሰው ላይ መከራን እንደሚያመጣበት መገለጡ
💜ምዕራፍ ፳፪፡-
-በእውነት መፍረድ፣ ቸር፣ የዋህና ቅን መሆን እንደሚገባ መገለጹ
💜ምዕራፍ ፳፫፡-
-በቃየል መንገድ መሄድ እንደማይገባ
💜ምዕራፍ ፳፬፡-
-ጌዴዎን እግዚአብሔርን በመታመኑ በጥቂት ሠራዊት ብዙ የአሕዛብን ሠራዊት ድል እንደነሣ
💜ምዕራፍ ፳፭፡-
-ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ የሚገዛና የሚያስተዳድር እግዚአብሔር እንደሆነ
-ደም ግባት፣ ገንዘብ ኃላፊ እንደሆነ መገለጹ
💜💜💜የዕለቱ ጥያቄዎች💜💜💜
፩. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. ድል መንሣት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው
ለ. በእግዚአብሔር መታመን ከጠላት ያድናል
ሐ. በእግዚአብሔር ከመታመን በሠራዊት መታመን ይሻላል
መ. በእግዚአብሔር የታመነ በሕይወት ይኖራል ይከብራልም
፪. እግዚአብሔር ሕጉን የማይጠብቅን ሰው ምን ያደርገዋል?
ሀ. በጠላቱ እጅ ይጥለዋል
ለ. ፍሬያትን በመስጠት ደስ ያሰኘዋል
ሐ. ዝናምን በጊዜው ያዘንምለታል
መ. ለ እና ሐ
፫. ጌዴዎን በጥቂት ሠራዊት በጣም ብዙ የሆኑ የአሕዛብን ሠራዊት ለማሸነፍ የረዳው ምንድን ነው?
ሀ. በእግዚአብሔር መታመኑ
ለ. ለጣዖታት መሥዋዕትን መሠዋቱ
ሐ. ኃይለኛና ጉልበታም መሆኑ
መ. ለ እና ሐ