አንደኛ መቃብያን ከምዕራፍ 21 እስከ ምዕራፍ 26

Поділитися
Вставка
  • Опубліковано 5 лют 2025
  • 💜 መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ክፍል 5 💜
    💜ምዕራፍ ፳፩፡-
    -ዳዊት በእግዚአብሔር በመታመኑ ከሳኦልና ከሌሎችም ጠላቶቹ እጅ እንደዳነ መነገሩ
    -ድል መንሣት ከእግዚአብሔር እንደሆነ መገለጡ
    -እግዚአብሔር ሕጉን በማይጠብቅ ሰው ላይ መከራን እንደሚያመጣበት መገለጡ
    💜ምዕራፍ ፳፪፡-
    -በእውነት መፍረድ፣ ቸር፣ የዋህና ቅን መሆን እንደሚገባ መገለጹ
    💜ምዕራፍ ፳፫፡-
    -በቃየል መንገድ መሄድ እንደማይገባ
    💜ምዕራፍ ፳፬፡-
    -ጌዴዎን እግዚአብሔርን በመታመኑ በጥቂት ሠራዊት ብዙ የአሕዛብን ሠራዊት ድል እንደነሣ
    💜ምዕራፍ ፳፭፡-
    -ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ የሚገዛና የሚያስተዳድር እግዚአብሔር እንደሆነ
    -ደም ግባት፣ ገንዘብ ኃላፊ እንደሆነ መገለጹ
    💜💜💜የዕለቱ ጥያቄዎች💜💜💜
    ፩. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
    ሀ. ድል መንሣት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው
    ለ. በእግዚአብሔር መታመን ከጠላት ያድናል
    ሐ. በእግዚአብሔር ከመታመን በሠራዊት መታመን ይሻላል
    መ. በእግዚአብሔር የታመነ በሕይወት ይኖራል ይከብራልም
    ፪. እግዚአብሔር ሕጉን የማይጠብቅን ሰው ምን ያደርገዋል?
    ሀ. በጠላቱ እጅ ይጥለዋል
    ለ. ፍሬያትን በመስጠት ደስ ያሰኘዋል
    ሐ. ዝናምን በጊዜው ያዘንምለታል
    መ. ለ እና ሐ
    ፫. ጌዴዎን በጥቂት ሠራዊት በጣም ብዙ የሆኑ የአሕዛብን ሠራዊት ለማሸነፍ የረዳው ምንድን ነው?
    ሀ. በእግዚአብሔር መታመኑ
    ለ. ለጣዖታት መሥዋዕትን መሠዋቱ
    ሐ. ኃይለኛና ጉልበታም መሆኑ
    መ. ለ እና ሐ

КОМЕНТАРІ • 2