Це відео не доступне.
Перепрошуємо.

"ዋለልኝ ለምን ለምን ሞተ?!” | የልጆቻችን ኢትዮጵያ | Ethiopia

Поділитися
Вставка
  • Опубліковано 19 гру 2019

КОМЕНТАРІ • 174

  • @maggiemaggie7009
    @maggiemaggie7009 4 роки тому +21

    እነዚህ ሁለቱ በጣም አደንቃቸዋለሁ ፣intelligent discussion 💯👌

    • @alfredoadam1703
      @alfredoadam1703 3 роки тому

      dunno if anyone gives a damn but if you're bored like me during the covid times you can stream pretty much all of the new movies on instaflixxer. Have been binge watching with my brother for the last couple of weeks :)

    • @luccaimmanuel7664
      @luccaimmanuel7664 3 роки тому

      @Alfredo Adam Definitely, been using InstaFlixxer for years myself :D

  • @gontelbelay8516
    @gontelbelay8516 4 роки тому +35

    እኔ በጣም የሚገርመኝ ሌላ እንቶ ፈንቶ የሚወራበት ቦታ የአድማጩ ቁጥር ብዙ ነው እነዚህን ሰዎች የሚያዳምጠው ሰው ከሚያስረዱት ቁምነገር አንፃር ሲወዳደር በጣም ትንሽ ነው ያሳዝናል ምን አይነት ማህበረሰብ በ27 አመት እንደተፈጠረ

    • @ritaa6260
      @ritaa6260 4 роки тому

      Gontel Belay, i am amazed too. i believe what they r talking is more than a kitchen table conversation. Also, many people are being blind due to racism. It takes an open mind and positive outlook to get it. BTW the panelists are great educators. I wish Dr. E listens more like today than cutting off Ato Yared.

    • @user-ll9jg5qy5p
      @user-ll9jg5qy5p 4 роки тому +2

      Gontel Belay እኑአም ድንቅ የሚለኝ ህብረተሰባችን ምን እንደነካው ነው። እነዚህ ሰዎች እያጠሩልን ያለው ነገር እጅግ ብዙ ነው። ወጣቱ ምን መስማት እንዳለበት የተምታታ ይመስለኛል።

    • @abrihambetta7021
      @abrihambetta7021 4 роки тому +2

      Exactly

    • @eluelu6166
      @eluelu6166 4 роки тому +2

      አፌ ቁርጥ ይበልልህ/ሽ።

    • @esatinternational1104
      @esatinternational1104 4 роки тому +1

      we have to share this

  • @gd8933
    @gd8933 4 роки тому +6

    የሚደንቅ ቃለ ምልልስ ነው:: እናመሰግናለን አቶ ያሬድ!! የበሰለ ትነታኔ ከሚነበብ የሀገር ፍቅር ጋ!!! ጃዋርን ለመሰሉ ለነዚህ ጥራዝ ነጠቅ ሀገር አፍራሽ ባንዳ ጋሎች በደንብ ስላስረዳህልን እናመሰግንሀለን!!!!

    • @ritaa6260
      @ritaa6260 4 роки тому +3

      Gezaw, please leave race and duregator word out of this. There are mean spirited people from every race and color.

    • @gd8933
      @gd8933 4 роки тому

      @@ritaa6260 you are right......

    • @ritaa6260
      @ritaa6260 4 роки тому +1

      @@gd8933 you are welcome my brother.

  • @fekaduyimer4697
    @fekaduyimer4697 4 роки тому +7

    ጥሩ ውይይት ነው እግዚአብሔር ሰላማቹሁን ይብዛላችሁ የኢትዮጵያ ልጆች

  • @muledele5262
    @muledele5262 4 роки тому +4

    በጣም ጥሩ ውይይት ነበር ይቀጥል የምንማረው እንዲህ ካሉት ሰዎች ጋር ጆሮ ሰጥተን ስንወያይ ብቻ ነው ዘር ላይ ያነጣጠረ ብቻ ከሆነ ግን ሌሎች ሚዲያዎችም ከናንተ ይማሩ ይቀጥል ይህ ዲስከሽን so interesting I like it let us go forward together keep it up

    • @gezualeme5856
      @gezualeme5856 4 роки тому

      For Dr. Ersido with humble respect I will suggest a book called "winners takes all " by Anand Giridharadas.

    • @gezualeme5856
      @gezualeme5856 4 роки тому

      For Dr. Ersido with hamble respect I will refer to you a book called "winners takes all "by Anand Giridharadas.

  • @Yoseph96
    @Yoseph96 4 роки тому +7

    Interesting. I could listen to you the whole day. KEEP IT UP 👍🏼

  • @jonijoni534
    @jonijoni534 4 роки тому +7

    ዋለልኝ የሚባል ሰይጣን ተፈጥሮብን ነው እነ መለስ የሚባሉ ጭራቖች ሊራቡ የቻሉት።i totally agree with you guys

  • @temesgentsegaye2048
    @temesgentsegaye2048 4 роки тому +5

    ውይይታችሁ:በጣም:ተመችቶኛል፣ዋለልኝ:የሚባለውን:አሸባሪ:በደንብ:ገልፃችሁታል፣ግን:ተደማመጡ፣ጉራማይሌ:ቋንቋ:በተቻለ:መጠን:አትጠቀሙ:ሌላ:መግለጫ:ቃል:ከአላጣችሁ:በስተቀር፣በተረፈ:ውይይቱ:በብሰለት:የተሞላ:ስለሆነ:በሰፊው:ብትቀጥሉበት:ደስ:ይለኛል።

    • @girmawoldemariam7107
      @girmawoldemariam7107 4 роки тому

      ውነት ብለሀል ዋለልኝ የሻቢያ ተላላኪ ነው

  • @berehaneghaile848
    @berehaneghaile848 4 роки тому +6

    ያሬድ የበስለ ተወያይ ነው ሊመስገን ይገባል።

  • @vitaethio6428
    @vitaethio6428 4 роки тому +2

    Thank you! We need more people like you.

  • @zekariasworku6387
    @zekariasworku6387 4 роки тому +8

    በዛሬው ውይይታችሁ ያነሳችሁት በጠቅላላ ማለት እችላለሁ ልዪ ነው👌🏽

  • @zemenlezemen6160
    @zemenlezemen6160 4 роки тому +7

    ውይይቱ አሪፍ ነው ግን አንድ ሰው ሃሳቡን ተናግሮ ሳይጨርስ ባታቋርጡ የበለጠ ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።

    • @frewabebe6891
      @frewabebe6891 4 роки тому

      በቂ ነዉ - ሁሉ መዘርገፉ ያሰንፈናል:: የተቀበልነዉን መርምረን የየራሳችንን የዳበረ ግንዛቤ እንድንይዝ ከረዳን..

  • @MyD1010
    @MyD1010 4 роки тому +1

    ሁለታችሁም ተወያዬች በሌሎች እርእሶች በተለይ በሥራ ፈጠራ ላይ የምታነሱት ሃሳብ ድንቅ ነው፣ በእዚህኛው በዋለልኝ መኮንን ላይ በተነሳው ሃሳብ ላይ ግን ብዙ እርቀት የሚያስኬድ ምርምር እና ጥናት የሚፈልግ ጉዳይ ነው እንጂ በተለይ ከአንደኛው ወገን እንደተነሳው እና እንደተሰጠው አይነት ድምዳሜ ላይ በቀላሉ መድረስ አይቻልም ብዬ አስባለሁ፣ ዛሬ ላይ ሆነን የዛኛውን ዘመን ሃሳብ ለመተቸትም ሆነ ለማጣጣል በቂ የሆነ ጥናት ማድረግ ይኖርብናል፣ የዋለልኝም ሆነ የእርሱን ትውልድ ሥራዎች ለማጥናት የሞከሩ ብዙዎች ባይኖሩም ጥቂቶች ሞክረዋል፣ ድምዳሜው ግን መደፍጠጥ ከሆነ አሁንም የሃሳብ ጨቋኝ ያስብላል፣

  • @user-ll9jg5qy5p
    @user-ll9jg5qy5p 4 роки тому +7

    "ዋለልኝ ለምን ለምን ሞተ" የሚለውን የያኔ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጥያቄ የዕውነት ይመስለኝ ነበር። አውሮፕላን ላይ በጥይት ሰው መትቶ እንደተገደለም አላውቅም ነበር። አሁን አሁን ግን ካደመጥኩት ሁሉ ዋለልኝ የኢትዮጵያ ጠላቶች የቀኝ ገዥዎች ቂም መወጫ ለመሆን ሲጣደፍ ሳያውቅ ሳይመረምር በደምፍላትና በግልፍተኝነት የኮሙኒስት አቀንቃኝ ሆኖ መሞቱን ሳውቅ ደሞ ለዋለልኝ ያለኝ ምልከታ ወደ ነጌቲቭ ወርዷል። ስለዚህ አውሮፕላን ጠልፎ ህዝብን ሊጨርስ ያለን መጥፎ ምሳሌ እንደ ታላቅ አርዓያ የሚያነሱ ሁሉ ቅዠታሞች መሆናቸውን ያሳብቅባቸዋል።እዚህ ላይ ለመጨመር ዋለልኝ አንድ ከወዳጁ ቆሞ የሚያወጋን ሸንቃጣ ጸረ-ጠላፊ ነው ብሎ በመጠርጠሩ ኢትዮጵያዊን " እጅ ወደላይ " ሲለው ወጣቱም(ባሁን ሰዓት በአሜሪካ የቨርጂኒያ ነዋሪ ናቸው፥ ደርግን ሸሽተው ከሃገር የወጡ) በቀላሉ እጁን ሳያነሳለት ሲታገሉ የዋለልኝ ሽጉጥ ተቀባብሎ ስለነበረ ጥይቱ የሚተናነቀውን ዋጣት እጅ ከሎሚው ላይ ቀንጥሶ ሲጥለው ጸረ-ጠላፊው በካራቴ ዋለልኝን ጣለው ፣ ማርታ መብራቱ የተባለችው ሌላኛዋ ጠላፊ ሽጉጥ ደግና ከኋላ ስትንቀረፈፍ ጸረ-ጠላፊው ከርቀት ባንድ ጥይት ቀልቧታል። ወዲያውኑ ዋለልኝንም እዛው ጨርሶት ሌሎችን ወደማደን ተንቀሳቅሶ አዳነች የምትባለው ብቻ ስትተርፍ ሌሎች ስድስቱን ቦምብ የወረወረውን ጨምሮ ጸረ-ጠላፊው ወዲያውኑ ጨርሷቸዋል።ምክንያቱም አየር ላይ ስለሆኑ ሁለተኛ ዕድል መስጠት ማለት አጠቃላይ ያውሮፕላኑን ተሳፋሩዎች መጨረስ ማለት ስለሆነና ጠላፊዎቹም ምን እንደታጠቁ ማወቅ ስለማይቻል ጸረ-ጠላፊዎቹ በሰለጠኑት መሰረት ህጋላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ትክክል ናቸው!!!ቢያንስ ለጊዜውም ቢሆን አደገኛ የናት የሃገር ጡት ነካሾችን መቀነሳቸው ታላቅ አርበኝነት ነው። ዕንደውም በህይወት ያሉ ካሉ ኢትዮጵያውያን ልንሸልማቸው ይገባናል።በዚህም የተነሳ አውሮፕላኑም በቦምቡ የመቀደድ አደጋ ቢደርስበትም በአብራሪው ጀግንነት ከ40 ሺህ ጫማ ከፍታ ላይ ለማሳረፍ ችሏል። ስለዚህ አንድ ተራ የሃገር ጠላት መጠቀሚያ የነበረን ዋለልኝ የተባለ የጊዜው አይሲስ የሚያቆለጳጵሱ የስብዕና ችግር ያለባቸው መሆን አለባቸው።አለበለዛም በዕብሪትና ማን አለብኝነት የራስን የዘረፋና የሌብነት ዕቅድ ለማስፈጸም የምትደረግ የተረኝነት አባዜ ነው ልትሆን የምትችለው።

    • @kassahunbayekedagn300
      @kassahunbayekedagn300 4 роки тому

      በትክክል አስቀምጠኸዋል የዛን ዘመን ታጋይ ነን የሚሉ የፈረንጅ ስራ አስፈጻሚዎች ናቸው።

  • @miheretuwuide1583
    @miheretuwuide1583 4 роки тому +2

    ተማርን በሚሉ መሃይማን መማርንና ማወቅን እዳልጠላሁት ሁሉ መማር እንደ እናንተ ከሆነ እውነትም ያኮረል ትውልድንም ያንፃል! በርቱልን
    ኢትዮጲያ ሃገሬ መሃፀነ ለምለም ናት!

  • @tesfut2863
    @tesfut2863 4 роки тому +5

    እንኳን ድብን አለ ምንም ሳይገባው አገሩን የገደለ

  • @tesfut2863
    @tesfut2863 4 роки тому +5

    በሳሎች ተባረኩ

  • @The_Man_from_toronto24
    @The_Man_from_toronto24 4 роки тому +4

    ውይይቱ እጅግ በጣም ድንቅ ሆኖ ሳለ አወያይ ሆኖ የተሰየመው ሰው ግን አንዱን ሃሳብ ሳይቋጩ ሌላ ጥያቄ በማንሳት በጥያቄ ላይ ጥያቄ በመጨመር ውይይቱን አንዛዝቶታል:: ለወደፊቱ የአንዱን ጥያቄ መልስ እልባት ሰጥተህ ወደ ሌላ እለፍ:: ተናጋሪዎቹ ንግግራቸውን እስኪጨርሱ ጊዜ ስጣቸው:: በሌላ ጥያቄ አታቋርጣቸው:: ምንም እንኳን ተያያዥነት ሊኖረው ቢችልም::

  • @solomonteffera1570
    @solomonteffera1570 4 роки тому +1

    Guys, i am addicted listening to you

  • @Ethiohabtina
    @Ethiohabtina 4 роки тому +2

    You guys are amazingly brilliant. I love the way you are talking even! So lovely! I live to listen to you! Keep it up! 💚💛❤️👌👍🙏

  • @AbrahamYayeh
    @AbrahamYayeh 4 роки тому +6

    መለስ ዜናዊ በህይወት ኖሮ ይቺን ቪድዮ ቢያዳምጣት ኖሮ መርዝ ሳያስፈልግ በደም ግፊት ይሞት ነበር፡፡

  • @abanav57
    @abanav57 4 роки тому +1

    ፕርግራሙ በተለይም የዛሬው የመወያያ ሃሳብ ድንቅ ነው።
    ይሁን እና ዋለልኝ ምንም እንክዋን ያመነበትና የሄደበት አቅጣጫ የተሳሳተ ቢሆንም የግለሰቡን intellectuality ዝቅ አርጎ ማቅረብ በሃላችን እና የኛ ኢትዮጵያዊዎች ባህል የሆነበት ዘመን ነው ያለነው።
    ዛሬ ዘመኑ አውቀትን ለማካበት ቴክኖሌጁው ቀላል አድርጎታል ፣ ዋለልኝ እና በጊዜው የነበሩት ታጋዮች በናንተ እና በማንኛውም አዋቂ የሚጣጣሉና እና የሚናቁ እንዳልሆኑ መታወቅ አለበት። ታሪክ ሰርተው የሄዱ ጀግኖች ናቸው።ንጉስን እንደአምላክ ከማየት ለማላቀቅ ሞክረዋል በጊዜውም ተሳክቶላችዋል።
    ምንም እንክዋን ለዛሬው ተረኞች ማጎብደድ እና ከፍ ከፍ ማድረግ የሃገራችን የሙሁሮች ጠባይ ቢሆንም።
    የእነኝህ ግለሰቦች ርእዮት አለም ከናንተ ይለያል ? Yes
    ርእዮተ አለሙ ለፓለቲካ መሪዎቹ እንደሚሆን ተደርጎ ተጠምዝዞ ተጽፍዋል ? አዎ
    መምታት ካለባችሁ በሚያሰምን ሁኔታ ጥሩ።
    እውቀታቸው እና ችሎታቸው ግን ከናንተ በጅጉ ይሻላል።
    ብሄር የለም የሚለውን ሃሳባችሁን በጣም አስማማለሁ፣
    በጊዜው ብሄርን በተመለከተ በአብዮተኞች ወይም በታጋዮች በኩል ከፍተኛ ውይይት እና ልዩነትም ነበር። በዚህም ምክንያት አንጃ ነት እና የፓርቲወች መፈረካከስ እንደነበረ ታውቁታላችሁ ይሁን እና የግለሰቡን ችሎታ እና እውቀት ለማጣጣል የምታደርጉት ሙከራ ሚዛናዊ አይደለም።
    የበሃል ልብሰን በተመለከተ እንደውም እንደ ኢትዮጵየ ህዝብ የሚለብስ የለም።
    በስራ እና casual ቦታ እንደምሳሌ ያቀረባችሁቸው ሀገሮችም አለባበሳቸው እንደኛው ነው።
    Struggle የሚለውን መጽሄት የምታወሩት እና የምታጣጥሉት ወደ ኸዋላ ተመልሶ በዛ ጊዜና ሁኔታ ላይ ቆማችሁ ከማየት የልቅ ከ50 አመት በህዋላ ባለው በዛሬው ጊዜ ተንተርሳችሁ ለማየት ነው የምትሞክሩት። እነኝ መጽሄቶች በጅ የሚሳሉ እና የሚታተሙትም በጊዜው ከሚገኙት ማሳተሚያ ቤቶች ዝቅ ያለ እንደነበረም መዘንጋት የፈለጋችሁ ትመስላላቸሁ።
    የስትራግልነ መጽሄት ከቨር በተመለከተ ይዘቱን እና the target and the motive ከማየት ይልቅ የሰነዘራችሁት ቃላት እናንተንም ዝቅ ያደርጋል።
    ለወደፊት ይሄንን አይነት attitude ይዛችሁ ባትቀርቡ ይመረጣል።

  • @asnakewbewketubelete4108
    @asnakewbewketubelete4108 4 роки тому +1

    Interesting discussion!

  • @aselefechgirma4908
    @aselefechgirma4908 4 роки тому +2

    በጣም ጥሩ ውይይት ነው።

  • @user-xk1bm3nk8j
    @user-xk1bm3nk8j 4 роки тому +1

    ዋው ደስ ይላል ስለዚህ ዋለልኝ ስለሚባል ስው ማወቅ እፈልግ ነበር አመሰግናችዋለው

  • @isanahmi8298
    @isanahmi8298 4 роки тому

    በእውነት ኢትዮጵያችን በሆዳቸው ባደሩ ሙሁራኗቷ አሁን ላለችበት ሁኔታ በቅታለች በዚህ ሰዓት እናንተን የመስለ በሁሉም ነገር ሙሉ የሆናቸው ድንቅና ማራኪ በሆነ አቀራረብ እውነተኛ ትንታኔ በናንተ ኢትዮጵያን በማየታችን እጅግ በጣም እንኮራባችኃላን በርቱ።

  • @user-ll9jg5qy5p
    @user-ll9jg5qy5p 4 роки тому +1

    ዶክተር የምታነሳቸው ሃሳቢች ብዙ ጊዜ የውጭ ኦንላይን ንግዶችና አገልግሎቶች ላይ ወጣቱ ተሳታፊ የሚሆንበትንና ለራሱም ለሃገሩም የሚጠቅምበትን ስለሆነ በታላቅ ክብር ነው የምንገነዘበው። ለመንግስት አካላት አወያይተህ አካሄድ ቢመቻች ትልቅ ውጤት እንደሚያስመዘግብ ዕሙን ነው።

  • @vitaethio6428
    @vitaethio6428 4 роки тому +4

    "ke intellectual ke diaspora lezich hager tesfa metebek sehetet newu" WOW

  • @user-jj3nu9kf5f
    @user-jj3nu9kf5f 4 роки тому +1

    ዶክተር አርሴዶና አቶ ያሬድ የሰጡት ትንተና እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል።
    1ኛ፣የዋለልኝ አድናቂዎች፣እነ ፕሮፌሰር ገብሩ ታረቀኝ፣ ተሰብስበው የተሳሳተ መረጃ ለጀነሬሽኑ ሲያስተላልፉ የነበረውን በአንድአፍታ ቀርቦልን እነሱን በፈረንጆች በ29 ኖቬምበር 2019 ተችተናል። አሁን ግን እነዚህ ምሁሮች ያንን ትችት በማስረጃ አብራርተውታል እናመሰግናለን።
    2ኛ፣ጋዜጠኛው የብሄር ጭቆናን ከመደብ ጭቆና ሊለየው ሲፈልግ ባጭሩ ይሰማል። ይህን አባባል እነ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴና መድሀኔ ታደሰ ከአመት በፊት ሲሉት ነበር። የብሄር ጭቆናና የመደብ ጭቆና የኮሚኒዝም የኮሌክቲቭ አስተሳሰብና ፣ሁለቱ ማለት ቀልቀሎና ስልቻ፣ከፋፋይ አግላይ፣የሰው መብት ገፋፊ አስተሳሰቦች ናቸው።
    3ኛ፣ በውይይቱ ወደ መጨረሻው አካባቢ ስለ ዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ስለ አሊባባ፣ስለ ሞኖፖል፣ስለ ስራ አጥነት፣ስለ ነፃ ገበያ፣ስለ ኮምፒቲሽን፣ስለ መንግስት ጣልቃ ገብነት በትንሹ ተነስቶ ነበር።
    በተመሳሳዩ ይህ ውይይት በኤል ቲቪ በ06 ዲሴምበር 2019 ወጥቶ ነበር። በዛም ልይ ሀሳብ ስራ አጥነትን በተመለከተ ሰንዝረናል። ይኸውም
    መንግስት በትክክል ስራውን ከሰራ፣ለሚቀጥሉት 40 አመታት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ቴክኖሎጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣የሞኖፖሎች ኢንቨስትመት፣ስራን፣ኮምፒቲሽን፣ሀብት ይፈጥራል ብዬ አስባለሁ።

    • @mesfinmekonnen7583
      @mesfinmekonnen7583 4 роки тому +1

      ስለምን ትንሽ ስዓት ብትጨምሩና ብትወያዩ ስንት የማይረባ ነገር እየተላለፈ ።በጣም ትምህርት ስጭ ነበር በርቱ!!!

  • @mulugetatessema
    @mulugetatessema 4 роки тому +1

    wow! GOD BLESS!

  • @gebermichaeltibebu4162
    @gebermichaeltibebu4162 4 роки тому +2

    Please, listen one another it helps us to get your opinions but your discussion is wonderful . thanks!

  • @kedirmohammedidris8140
    @kedirmohammedidris8140 4 роки тому

    የሀገራችን የፀጥታ ኃይል የእነ ዋለልኝ መኮንን ላይ እርምጃ ከወሰዱ ጀግኖች መማር አለባቸው። ገና ለገና ከኦፕሬሽን በኃላ ተጠያቂነት ብለው መሸማቀቅ የለባቸውም።

  • @samiya6526
    @samiya6526 4 роки тому +1

    ስለ ዋለልኝ ታሪክ መስማት ይመስጠኛል ከዚህ bfite art tv ላይ ደረጄ ሀይሌ ብዙ እንግዶች ጋብዞ አዳምጫለሁ እዚህ ላይ ጊዜዪን ነው ያቃጠልኩት ፣ ትንተና ቁምነገር ይጨበጥበታል ሌላው ቢቀር ስለ አማማቱና ዘሮፕላን ውስጥ የነበረው ግብ ግብ በደንብ ማቅረብ ነበረባቹ ካጠፋው ልጥፋ

  • @malcolmx1280
    @malcolmx1280 3 роки тому

    these channel is the best one. i dont no why many ppls doesnt watch these than galamale of others

  • @ethiopiaethiopia8772
    @ethiopiaethiopia8772 4 роки тому +3

    መንጋ
    ጩኸት ከለለው የዚህ አይነት ውይይት አይመቻችሁም
    ገባ ገባ በሉና አብረን እንጠጣ?

  • @zelalemtadesse
    @zelalemtadesse 4 роки тому

    እጅግ ግሩም ውይይት ነው። በርቱ። እንደዚህ አይነት ውይይት ለአገር ብዙ ጥቅም ይኖረዋል። በተለይ የዋለልኝ ጉዳይ እንቅጩን መናገራችሁ ደስ ብሎኛል።

  • @user-ll9jg5qy5p
    @user-ll9jg5qy5p 4 роки тому +3

    ዶክተር ጓደኛህ ሲናገር ሃሳብህን ማስታወሻ ያዝና ምንም ሳታስቀር ከሱ በኋላ ከነትችትህ ሙሉ ሃሳብህን ብንሰማ። ምክንያቱም አንተም ጋር ያለውን ጓደኛህም ጋር ያለውን ሳይቆራረጥ ለመስማትና ሙሉ ሃሳብ እንዲኖረን ይረዳል ብዬ ስላሰብኩና ጠቃሚ ሃሳብ እንዳያመልጠን ነው።

  • @Yoseph96
    @Yoseph96 4 роки тому +5

    I love you guys but please don’t interrupt each other as its difficult to follow what you are saying.

  • @vitaethio6428
    @vitaethio6428 4 роки тому +3

    "ke university ena high school jemero yenebere tera besheshek lezi astewatso aladeregem belachehu tasebalachehu?" VERY TRUE!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

  • @betiyabebe9266
    @betiyabebe9266 4 роки тому +2

    Wow helam asetemar nahcew ewedahcehalew 👏👏👏

  • @lamrof
    @lamrof 4 роки тому

    ራሰበራው ሰውዬ የሚናገረው ፍሬ ነገር ሆኖ ሳለ፣ ሳይቸግረው ወደ እማይችላት እንግሊዝኛ እንደሚሄድ አልገባኝም። እኛ እዚህ አሜሪካ ለረዥም አመታት ለኖርነውና የዓማርኛን ልዕልና ለመሰከረነው ስቅጥጥ ያደርገናል። ሲጀመር እንግሊዝኛው ያስቃል፣ ሁለተኛ ይህ መናኛ ቁርጥርጥ ያለ አስቂኝ እንግሊዝኛ እንዲህ ጥሩ አይምሮ ካለው ሰው አፍ ሲወጣ በአዳማጭ ዘንድ የሚጣረስ ስሜት ያሳድራል።

  • @TADESDR3
    @TADESDR3 4 роки тому

    ዶ/ር አርሴዶ ልክ ነህ፣ አሁን ሰርተን ልዩነትን ማጥፋት ባለብን ግዜ ላይ ልዩ ዓይነት intellectualism የተፈጠረ ይመስላል፣ኁዋላ ቀርነት ነው፣አሁን ሰለነዋለልኝ እያነሱ የህዝብ ዓዕምሮን መበረዝ ምን ይሉታል?

  • @loveall360
    @loveall360 4 роки тому

    ሰዎቹ ጥሩ ተወያይ ናቸው ኢሄን ቀዥቃዣ ጋዜጠኛ ግን መላ ቢፈልጉለት ጥሪ ነው።

    • @mounttossa9136
      @mounttossa9136 3 роки тому

      Betam...Both of them are great individuals

  • @biniyamgirma5971
    @biniyamgirma5971 4 роки тому +1

    Er yebahil libese rasu yetu new bezaw mahiberesebe kirena kulefe yetesera. Thanks for recommending ato sebesebe book I love it.kechalachu gabezut nurulegn

  • @zerfiedejene7186
    @zerfiedejene7186 4 роки тому

    በውነት የናንተ ውይይት ጥሩ ነው ነፃ ሆናችሁ እቤታችሁ ቁጭ ብላችሁ በተለያዩ ጉዳዮች እምታደርጉት ንግግር ይመስላል ስትተራረቡ እራሱ ጏደኛሞች የሚያደርጉት ቀለል ያለ ምክር ለበስ ነው ደስ ይላል ውይይታችሁን እንድንናፍቅ አድርጋችሁናል ቀጥሉበት እባካችሁ?

  • @YET64
    @YET64 4 роки тому

    Great discussion

  • @berehanbehonegn136
    @berehanbehonegn136 4 роки тому +1

    ዋለልኝ የሞተው በወንጀል ተግባር ተሰማርቶ የኢትዮጵይ ሀብት የነበረ አውሮፕላን ለመጥለፍ በውስጡ የነበሩት ተሳፋሪዎች ለከፍተኛ አደጋ ምን አልባትም የሞት አደጋ ወንጀል ለማድረስ ሲል ተሳፋሪዎችን ለማትረፍ ሲባል በተተኮሰበት ጥይት ተመቶ ነው::

  • @yetinayeteshete5220
    @yetinayeteshete5220 4 роки тому +1

    Keep it up 👍

  • @mesfina.4153
    @mesfina.4153 4 роки тому

    ስለዋለልኝ ያቀረባችሁት ተመችቶኛል። እንዲህ ነው እውነቱ መነገር ያለበት። እንዲያውም በቅርቡ በደረጀ ሀይሌ ፕሮግራም ላይ አይሮፕላኑ ሲጠለፍ የነበሩ ሰው መፀሀፍ ፅፈው አቅርቧቸው ነበር እና ስለአሞሟቱ ይናገሩ የነበረው ፓለቲከኞቹ ሲነግሩን ከነበረው ሙሉ በሙሉ የተለየ ነበር። በርቱ የውሸት ትርክቶችን እንደዚህ አጋልጡ።

  • @ketemayerga5623
    @ketemayerga5623 4 роки тому +2

    Wow 🔥🔥🔥

  • @JoJo-uo9ep
    @JoJo-uo9ep 4 роки тому +1

    የተብራራ መረጃ ደረጀ የሚያቀርበው ፕሮግራም ላይ የአይን እማኝ አቅርቦ የተናገሩት አለ ተመልከቱት አርትስ ቲቪ ላይ በነገራችን ላይ የሚለው ፕሮግራም ላይ ለመረጃ ያክል ነው ።

  • @lamrof
    @lamrof 4 роки тому

    ደቂቃ 28:20 አንጀት የሚያርስ ድንቅ የሆነ ንግር አዳመጥኩ። «እኛ ኢትዮጵያውያን ከዳያስፖራውና ከልሂቃኑ ለዚህች አገር ተስፋ መጠበቃችን ስህተት ነው። እኛ ኢትዮጵያውያን ብድቅ ብለን የልጆቻችንን ኢትዮጵያ ጉዳይ እጃችን ላይ ማምጣት አለብን።» ስማ ወገኔ ሆይ !

  • @yedesdeswebetu2860
    @yedesdeswebetu2860 4 роки тому +2

    Thank you, all your discussion on Ideas are really enlighting. But I still insist the moderator must come with good preparation and questions with substance, otherwise, he can't escape the criticism of ቁንጽላዊነት...

    • @ritaa6260
      @ritaa6260 4 роки тому

      I like that "ante lij selehonk new.".

  • @ayeleasfaw783
    @ayeleasfaw783 4 роки тому +1

    Do you know where the Majesty bring the child to learn the contemporary learning

  • @abz8493
    @abz8493 4 роки тому

    ማፍቀር ለተሳነው ሃገሩ ሸቀጥ ናት
    ★★★★★★★★★★★★
    ዕልፍ ሰማዕታት፣ በደም በአጥንታቸው፣ ገድል እየሰሩ፣ ያቆዩትን ሃገር
    በሃገሬው ተስፋ ላይ፣ በእውኑም በህልሙም፣ እያለመ መንበር
    በጎጡ ተጠምዶ፣ ትውልዱን ለሚያምስ በቋንቋ በብሄር
    በእይታው ልክ ጠቦ፣ አንድነት ሰባኪን፣ አስፊውን ለሚያጠብ
    ሃገሩ ጥገት ናት፣ በብሄርተኛ ዓይን በጉግማንጉግ ምናብ
    እንደ አሜሪካ ላም፣ ቀን ሌት ምትታለብ።
    ስለምን ከማይል፣ እስከ ግበረ አበሩ፣ እያለመ ወንበር
    በትውልድ ህልም ላይ፣ ቁማር ለሚቆምር
    በጥቅም ተጠምዶ፣ ወገኑኑን ለሚያምስ በክልል በሰፈር
    በእከከኝ ልከክልህ፣ በአምቻ ጋብቻ፣ በወንዝና መንደር
    በእይታው ልክ ጠቦ፣ አብራከ ተስፋ ሚነጥቅ፣ ታታሪን ለሚያሰንፍ
    የዜጋውን ዕራይ፣ ሃገር ማበለፀጉን፣ ጥረቱን ለሚነቅፍ
    በሰማዕታቱ በአበው ታሪክ ደምቆ፣ ቅድመ አያት ለሚዘልፍ
    ለልጅ ልጅ እንዲያወርስ፣ ከተሰጠው ሀገር፣ አኩሪ ታሪክ ሚቀጥፍ
    ጠኔ ከሚያላጋት፣ ከታረዘች ሃገር፣ በስም ተመፅውቶ፣ ያለ ሃፍረት ለሚዘርፍ
    ያለ ርህራሄ፣ በዘቀጠ ሞራል፣ የብሄር ጭብል ለብሶ፣ ልዩነት ለሚለፍ
    በጎጠኛ አዕይምሮ፣ በጉግማንጉግ መዳፍ
    በአስመሳይ አንደበት፣ ሚዛን ያልጠበቀ፣ ትርክት የወለደው፣ ማኒፌስቶ ቢፃፍ
    በጩኸት ተሞልቶ፣ በአሽቃባጭ ዘጋቢ፣ ምን ቢኮለታተፍ
    በበቀል ተቋጥሮ፣ ዘመን የማይመጥን፣ ወንዝ የማይሻገር፣ ዕራይ ለተለመ
    ሀገሩ ሸቀጥ ናት፣ በተዛባ ትርክት፣ ማፍቀር ለተሳነው፣ ወስጡ ለታመመ።
    በቸርነቱ ይጎብኘን!!!

  • @asfawgetachew713
    @asfawgetachew713 4 роки тому

    Thanks to Dr.Ersido ,Mr.Sebesibe and Andafta media the over all program of such discussion can be considered as an online education and lecture that the new Generation of Ethiopia has got an opportunity to learn from and update his knowledge to the new world thinking than the legacy of Walelegn Mekonne ethnic politics & selfe determintion .

  • @yisehakuk
    @yisehakuk 4 роки тому

    ዶክተር ኤርሲዶ የሚመጣልህን ሃሳብ ያዝ አድርገህ ለመቆየት ሞክር እንዳንድ ጊዜ ሌላውን ሰው ታቋርጣለህ:: እኔም ተመሳሳይ ችግር አለብኝ:: በተረፈው ቀጥሉበት በጣም የሚያስተምር ነው:: እናመሰግናለን

  • @yosephchenkew7227
    @yosephchenkew7227 4 роки тому

    ዕውነታውን ሥለነገራችሁን እነመሠግናለን

  • @1benyam1
    @1benyam1 4 роки тому

    ምርጥ ውይይት ነው ቀጥሉበት፡ ግን ሰፋ ያለ ጊዜ ብትወስዱ ደስ ይለኛል፤ ቶፒኮቹ በጣም አሪፍ ናቸው፡ ግን በሀምሳ ደቂቃ ሚፍታቱ አይደሉም እና ልጅ ቢኒ አስብበት አወያይ ስለሆንክ ባንድ ኪሎ ፌስታል መቶ ኪሎ መጠቅጠቅ እንዳይሆን፤ በደንብ ስትከራከሩ ባይ ደስ ይለኛል፤

  • @felekeshebeta3756
    @felekeshebeta3756 4 роки тому +1

    ተደማመጡ። አንዳችሁ የጀመራችሁት ሀሳብ ሳትጨርሱ ጣልቃ አትግቡ።
    አቶ ያሬድን ያላስጨረሳችሁት ሀሳቦች አሉ።ተመልሳችሁ ብታይዋቸው መልካም ይመስለኛል እነዚህም አንደኛው ከአድዋ ድል በሁዋላ ፈንጆች ስለፃፍዋቸው መፅሀፍቶችና ስለ ተናገሩ ሰዎች ተናግረው ሳይጨርስ ወደ ሌላ ወሰዳችሁዋቸው።
    ሁለተኛው የእነ አሊ ባባ አይነቱ ጉዳትም እንዳለው እያብራሩ ስለነበረ ይጨርሱት።በነገራችን ላይ ይህንን ቴክኒዮሎጂ አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ጀምሮት ነበር ይባላል።

  • @Humanity-info
    @Humanity-info 4 роки тому

    ጤና ይስጥልኝ ዶ/ር ኤርሲዶ ፕራግራማችሁ አስተማሪ በመሆኑና የማስበውን የምታስቡ የምናገረውን የምትናገሩ አይነት ሆኖ ስለተሰማኝ እከታተላችኋለሁ ወደፊትም እከታተላለሁ። አንዳንድ ቃላትና አመለካከት ላይ ኝ ትንሽ ጥንቃቄ ብታደርግ ጥሩ ነው፡፡ ይቅርታ ብትጠይቅም መልካም ነው። በዚህ ከቀጠልክ ቦዲ ጋርድ ሊያስፈልግህ ነው!!! ዋለልኝን የወቀጣችሁበት ሎጂክ እና ፋክትስ ተስማምተውኛል።አብሬያችሁ ብኖር ኖሮ እኔም አፍንጫ አፍንጫውን ነበር የምለው። በ18 ዓመቴ ልቤን ነስቶኝ የገባሁበት የኮምኒዝም አምልኮ 6 አመት በእስር ሲያንገላታኝና አንተ ዛሬ ከዶ/ርነት ወደፕሮፌሰርነት የምትሯሯጥበትን እድል ሳላገኝ የቀረሁት በነፍስ አጥፊነት ወይንም በወንጀለኛነት ስሜት ሳይሆን በታጋይነት ነው። ታሪኩ ረጅም ነው። ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም እንደሚለው ሳይሆን በህጻንነቴ የተመኘሁለት የህዝብ ዴሞክራሲያዊ መብት አልተከበረም በሚልም እስካሁን ካለሁበት ዳያስፖራ ስለሃገሬ ጠዋት ማታ እያሰብኩ ነው። ከዚህ አነጋገርህ እንደምረዳው ዳያስፖራው ነፍሰ ገዳይ ነው! በሃገሩ ጉዳይ አይመለከተውም ወይንም አንተና እንዳንተ አይነት አስተሳሰብ ያላቸው ወይንም ደግሞ ቀደም ብሎ ደም የሌለበትንና ደረቅ ደረቁን ይረግጡ የነበሩ ሰዎች ብቻ ስለዛች ሃገር ማሰብ የሚችሉት ማለት ስህተት ይመስለኛል። እንዳው ሳየው ነገሩ አብዮቱ ፈንድቶልህ "እብድና ዘበናይ የልቡን ይናገራል" አይነት ሆኖ ነው እንጂ ቀደም ብሎ የተጓዝክበት የትምህርትና የህይወት ልምድህ ይህን ሳያሳውቅህ የቀረ አልመሰለኝም። በውርጋጥነት ዘመናችን በውል ሳናውቀው "አለም በሁለት ተከፍላለች ወደፊት ግን ..." እያልን እናቦካው የነበረው ኮምኒዝም ዛሬ ተሳክቶለት ቢሆንና የካፒታሊዝም አራማጆችን ድራሻቸውን አጥፍተን ዶ/ኤርሲዶም ኩሊው የዋርካውም እኩል የሚበሉበት የሚጠጡበትን ስርዓት በፈጠርን። አንተም ዛሬ ኮምኒዝም የመጣልህ ነህና ከውጤቱ ተቋዳሽ በሆንክ። ህልማችን ይኸው ነበረ። መኖር እየተቻለ ዋለልኝም ሆነ እኔ "ያልበላንን ባላከክን" ። ፕሮፌሰር እከሌ እየተባልን ደልቶን በህይወት በኖርን ነበረ። ወያኔ ህዝባችንን ሲያሸው የት ነበርክ ለሚለው ጥያቄ ያንተን ምላሽ ባላውቅም እኔና የያኔው የታጋይነት ልክፍት ያለቀቀን ዳያስፖራዎች ቢያንስ ላለፉት 22 እና 23 አመታት ጊዜያችንንና ገንዘባችንን ህዝባችን በሃገር ቤት ለሚያደርገው ትግል ስንከፍልለት፣ ስናስተባብር በየመንግስታት ቢሮው ስንጮህ ከርመናል። ዛሬ እነከበቡሽ ጥልቅ ብለው "ዋለልኝ ለምን ለምን ሞተ" እያሉ ድላችንን ቢቀሙንም እኛ ዳያስፖራዎች ለዓመታት የነከበቡሽን ወሽመጥ በመቁረጥ ሃይላንድ ውሃ ምላሳቸው ላይ አንጠልጥለንባቸዋል። ጊዜ ሲኖርህ አንድ ጥሩ ተሞክሮ ያለው ዳያስፖራ ፈልግና አንድ ጥግ ላይ በዳይቡሹ ቡና አንብበው። ይነግርሃል። በተረፈ ዛሬ አብዮቱ ስለፈነዳልህ እየተነሳህ አታፈንዳን። ስትዳኘን ያኔን ሆነህ ብትዳኘን ስትፈርድብንም ያኔ ልክ በጊዜው እንደነበርክ ሆነህ ብትፈርድብን ምንኛ ደስ ባለኝ ነበር። ሃገራችን ወደፊት ማደግ ሲገባት የኋሊት የጎተተንን ኮምኒዝም ያመጣብን ደርግ ነው የሚል የመሃይም ድምዳሜ ውስጥ እንደማትገባ ተስፋ አደርጋለሁ። ደንቆሮውን ወታደር ጎትቶ ኮምኒዝም ውስጥ የጨመረው የተማረው ነው ከማለት አልፌ እንዳው እኮ ፈርዶበት ነው እንጂ ወታደር እኮ የንጉስ ባለሟል ነው። "ንጉሱ ለዘለዓለም ይኑሩ" ብሎ ኮፍያውን ወደሰማይ እንዳሽቀነጠረው ከንጉሱ ጋር አብሮ አየገደለ ማዕረጉን ከፍ እያደረገ፣ ጫንቃውን እንደኮርማ እያሰባ ከሞት ከእስርና ከስደት ነጻ ሆኖ በኖረ እስከማለት እደፍራለሁ። ቁርሱን በልቶ ምሳውን ከማይደግም ቤተሰብ የወጣውና በሞት የተለየው፣ በእስር የተንገላታውና በየበረሃው ለትግል የነጎደው ወጣት በዋለልኝ በራሪ ወረቀት ወይንም በማናቸውም የፖለቲካ ፕሮግራም ምክኛት ቢሆንም በነፍስ ቆርጦ ለሌላው ለመሞት ራስን አሳልፎ መስጠት የሚያኮራ ተግባር ነውና ባናወድሰውም በቆረጣ አየት አርገን እንኳን ብናልፈው የተገባ ይሆናል ብዬ እምናለሁ። በሌለ የብሄር ጭቆና ረሃብተኛ ሰብስበው በመሸፈት መከራ ያበሉንን 7 የትግራይ ወሮበሎች ግን አይጨምርም።
    መልካም ፕሮግራም

  • @korechogeleta9138
    @korechogeleta9138 4 роки тому

    Guys,God bless you!!!!You exposed these modern ignorants from the sixties!!!!

  • @abz8493
    @abz8493 4 роки тому

    " ነፃ አውጭዎቻችሁ እኛ ነን እያሉ ነፃነቱን ከሚነፍጉት ሞራለ ቢሶች፣ ነፃነቱን በተስፋ የሚጠብቅ ዜጋ ከቁራ መልክተኞችም ከራሱም በፍፁም ነፃ አይወጣም።
    ምክንያቱም ወደዚች ምድር ሲመጣ በቅድመ አያቶቹ የተከሰሰ አጥንትና የፈሰሰ ክቡር ደም ነፃነቱ ከትውልድ ትውልድ ሲወራረድ እንደመጣ ሊዘክሩለትና ሊያስተምሩት በማይሹ የባህድ የሚስጢር ኪስ የእናት ጡት ነካሾች በለጋ አዕምሮው ያልበር ማንነትና ጥላቻ በተቀነባበረ መልኩ ሲግቱት ነፃ ሆኖ የመፈጠሩ ስብዕና በዕቡ ጉግማንጉጎች እኩይ አስተምሮ እንደማይታደለው አስረግጦ ባለመናገሩ ነው።
    ይኸንንም አይቶ እንዳላየ የሚያይ፣ እስኪያልፍ ያለፋል እያለ፣ የሚተክዝን ዜጋ፣ ትግስትና አርቆ አስተዋይነቱን፣ እንደ ፍርሃት በመቁጠር፣ ጥበት፣ የበታችነት ስሜትና ስብዕና የተጠናዎታቸው ፣ ራዕያቸው ከሃገር ልዑዓላዊነት፣ ከወገን ደህንነትና፣ በሳላም ውሎ ማደር ይልቅ፣ በጎጥ ዙሪያ፣ የልዮነት ሹርባ እየጎነጎኑ፣ ድርና ማግ ሆኖ ሚኖር ህዝብን፣ በማይቆም የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መክተትና፣ የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ሰላምና ብልፅግና ማይሹ ባህዳንን፣ እኩይ ተልዕኮ ማስፈፀምና፣ ባፈናቀሉት ወገን ስም፣ ምፅዋት መሰበሰብና፣ የህገወጥ መሳሪያ ደላላ ሆኖ፣ የስልጣን ዘመንን ማራዘምና፣ ቀፈትን መሙላት ነው።
    ለዚህም ተልዕኳቸው ደግም፣ ለምን እንዴት ስለምን፣ ወዴት ለማን ብለው የማይጠይቁ፣ ሩጠው ያልጠገቡ፣ የነገ ሃገር ተረካቢዎችን ህይወት፣ እስቀማስቀጠፍ እኩይ ሴራ ያሴራሉ። "
    ***********************
    ፍቅር እስክንገዛ
    ★★★★★★
    እንደ ዕንቁ እያየቸኝ፣ በእናትነት አይኗ ተመስጣ ሀገሬ
    እንደ ልብህ ቦርቅ፣ እንዳሻህ ኑርባት በቅድስቷ ምድሬ
    ብላ ስትነግረኝ፣ ከጎና አስቀምጣ፣ ፍቅር እየመገበች በእጆቿ ለፀጉሬ
    መች ህልሜ እውን ቢሆን፣ ብመረቅ ተምሬ
    በክልል ሸንሽኖን፣ የአንችው እኩይ ፍሬ
    ብየ መልስ እንዳልሰጥ፣ ለእምየ ለፍቅሬ
    በደሌን ስሰማ፣ ልቧ እንዳይሰበር፣ ሃዘኗ እንዳይበዛ
    ከወንድም ተፋልሜ፣ ክብሯን እያስጠበኩ፣ ለአብራክ አምባገነን፣ ለሴራው ልገዛ
    እሱ ጎጥ አቅሮት፣ እኔም በፀሎቴ፣ ፍቅር እስክንገዛ።
    በየአቅጣጫው ለሚፈናቀሉ፣ በየትምህርት ተቋሙ ለሚሞቱ፣ የብሄር ፖለቲካው ሰለባዎችና ለኢትዮ ኤርትራ ተጎጅዎች።
    ***************************
    የአዳም ዘር እንደምን አለህ???
    ★★★★★★★★★★★
    በአያቶችህ ቅን ባህሪ፣ ፍቅራቸው ተኮትኩተህ
    ግን በእስተርጅናህ የማስተውል፣ ስብዕና የሸሸህ
    የብሄር ዱለት ዶልተህ፣ በቅጥፈትህ ያነታረክህ
    ማህይም የምትባል፣ በእውቀትም የበለፀግህ
    ገንዘብ ዕንቁ በስም መግነን፣ ከፍቅር በላይ የተመኘህ
    በዚች ምድር ላይ፣ መቸ መጥተህ
    መቸ እንደምታልፍ ማተነብይ፣ በእጅግ ማወቅ የተሳነህ
    ያለ ጥሪት እንደመጣህ፣ ማትቀበር ከነዝናህ ቅራቅቦ የቤት ዕቃ፣ አልማዝ ዕንቁ፣ ወድ ንብረትህ
    ወዳጀ የአደራ በግ፣ የአዳም ዘር አንደምን አለህ።
    ***************************
    እናርጅና እንጥበብ
    ★★★★★★★
    ቄሮ ፋኖ ዘርማ፣ ወጣት እያስቀጨን
    ከሞት ከሽረቱ፣ ወሳኙ ፍልሚያ ላይ፣እኛ እየተደበቅን
    በብሄር በሄረሰቡ፣ በስሙ ቀፍለን
    በግፍ ሚፈስ ደሙ፣ ስም ዝና እያካበትን
    ወንዝ ማይሻገር፣ ጎጥ ዕራይ ተለመን
    የነገን ናፋቂ፣ ህልም ተስፋ እየነጠቅን
    ወንበር አደላድለን፣ ሀገርን ያስወሸምን
    ከዘመን ማዕዱ፣ አትርፎ የቸረን
    በእድሜ ባለፀጎች፣ በጥላቻ ያበጥን
    ለምርኩዝ አብቅቶን፣ የማንል ተመስገን
    በሰማዕታቱ ገደል፣ በስማቸው ምለን
    በመጦሪያ ዘመን፣ በራስ ቃል የረከስን
    አደራ የበላን፣ ቃል ኪዳን አፍረሰን
    ከኸርማን ኮኸን ጋር፣ በእናት ሀገር ያሴርን
    ወገን የምንቀጥፍ፣ ካዝና እያስበርን
    አብራክ በዕዳ ምናስር፣ ከአብራክ
    እየዘረፍን
    በታሪክ ውስጥ አልፈን፣ ትውልድ አይዘክረን
    ገባ ገባ በሉ፣ በጎጥ እንቧደን
    እንቆቅልሽና፣ የአፍ መፍቻ ተረቱን
    ምናውቅልህና፣ ደግሞ የላም በረቱን
    እንቀይረውና፣ በእኩይ ተንኮላችን
    ለሚመጣው ትውልድ፣ የተዛባ ዶሴ፣ ታሪክ እናነብንብ
    በእዳ የተያዘ፣ የተዘረፈ ሃገር፣ በዕቡ እናስረክብ
    በመጦሪያ ዘመን፣ እንናርጅና እንጥበብ
    ውስኪ እየተራጨን፣ በደም እንታጠብ።
    *************************
    " Very few people really care about freedom, about liberty, about the truth, very few. Very few people have guts, the kind of guts on which a real democracy has to depend. Without people with that sort of guts a free society dies or cannot be born."
    Doris Lessing, the Golden note book.
    *********************
    ሗላ ቀር ይሉናል
    ★★★★★★
    የቅኝ ገዥወቻችሁ፣ እንዲፈፀም ቃሉ
    ታሪክ ምታውቁ እንጅ፣ ለታሪክ ማትውሉ
    ስልጣን ፈላጊዎች፣ ገባ ገባ በሉ
    እስኪ ደስ ይበለን፣ ከልብ ተማማሉ
    ብለው አማምለው፣ ብሩህ ተስፋዎችን
    በለጋ አዕምሮቸው፣ ግተው ቂም በቀለን
    ያልነበር ማንነት፣ በብዙው ሚጠላ
    አዳውረው አዳምጠው፣ በመፍተል በመላ
    ጎጥ አምላኪ እንዲሆን፣ አገር እንዲጠላ
    ለትውልዱ ቀርፀው፣ እኩይ ፍልስፍና
    ከመሳሪያ ጋራ፣ ተዘርቶ ማይበቅል፣ ስንዴ ሰፈሩና
    እኛ ስንቧጨቅ፣ እነሱ ይዘርፉና
    በርሃብ ጦርነት፣ እጅግ ተጎሳቁለን፣ ስንወድቅ ከጎዳና
    ፈጥኖ ደራሽ ሁነው፣ በአዲስ ስብዕና
    ብድር ለማበደር፣ ከፊት ይቆሙና
    ጥሬ ሃብት ለመዝረፍ፣ ይሽቀዳደሙና
    ህልማቸው ሲሰምር፣ በአንክሮ ያዩና
    በእኛ አጎብዳጅነት፣ ባህሪ ተደንቀው
    ሗላ ቀር ይሉናል፣ የምፀት ሳቅ ስቀው።
    ********************
    ምናሳፍር ፍጡሮች

  • @tinalove7727
    @tinalove7727 4 роки тому +1

    መልሱ፡ በደንብ ሳይዘጋጅ አውሮፕላን ሊጠልፍ
    ሲል ሞተ፡፡

  • @berhanumekonnen146
    @berhanumekonnen146 4 роки тому

    እኔ በብዙ ነገር ከአቶ ያሬድ ጋር እስማማለሁ ዓለምን እየተቆጣጠሩት ያሉት ዲጅታል ወርልድ አብዮት እንዳያስነሳ እሰጋለሁ ዓለም በጥቂት ግለሰቦች ቁጥጥር ስር እየገባች ነው ስለዚህ የሰው ልጅ መሸሽያ እንኳን እንዳይኖረው ሶስተኛ ዓለም ሀገሮችን ለመቀራመት መምጣታቸውን እንዳትረሱ የጉልቱን ተውት ነጋዴ በኢትዮጵያ አይኖሩም እነ አማዞንና አሊባባ ስራ ከጀመሩ ሁሉም ወደዲጅታል ይቀየራል
    የምታስፈራ ዓለም እየመጣች እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል ::

  • @harunbeshir8443
    @harunbeshir8443 4 роки тому

    ሱፍ ያደረገው በጣም ደስ ይላል።

  • @alexamanu9423
    @alexamanu9423 4 роки тому +2

    እ/ር ጨምሮ ጨምሮ አይምሮአችሁ ይክፈት ህዝቡ እናንተን ቢያደምጥ ከሰፈረት የብሄር ሴይጣን ይፈወስ ነበር።

  • @temesgenafework7280
    @temesgenafework7280 4 роки тому

    በጣም ደስ ይላል:: ዋለልኝም ተናግራል እኮ የጋራ ውጤት ነው ብላል፡፡ ሌላው እኔ እንጃ ሲአኤ አለበት ሚባለው ውሸት ይመስለኛል ዋለልኘኝ ንግግሩን ሲያጠቃልል እምፔራሊዝም ይውደም ብላል ሌላው ደግሞ የኮሚኒዝም አፍቃሪ ነው ዋለልኝ

  • @sarahbay3607
    @sarahbay3607 4 роки тому +1

    The man in blue tigree new malet new yewalelingn credit lenech mestete yifeligal tebaboch confidence yelachewum

  • @teddybel1539
    @teddybel1539 4 роки тому

    እንኳን ድብን አለ

  • @derejedejene9519
    @derejedejene9519 4 роки тому +2

    Dr Arsido, human beings do not live by bread alone. It looks like you just live to earn money and fill your stomach. You can air out your view, but doesnt have the right to insult a nation.

    • @kedirmohammedidris8140
      @kedirmohammedidris8140 4 роки тому

      ብሄር የሰደበ የለም። የቀረው ሙዚየም ማስቀመጥ ነው። በዘረኛ ዘመዱ የሞተበት እነኳን አይሳደብም።

  • @million3056
    @million3056 4 роки тому

    ስለ ዋለልኝ የመጨረሻ ሰዓት ከታች ያለውን link በመጫን ይስሙ። ua-cam.com/video/bcDWWEZePbw/v-deo.html

  • @DawitGAyele
    @DawitGAyele 4 роки тому +1

    Ethiopian air lines is hijacked 3 times by crazy people walelign and his group, the one crashed in Comoros, the c/o pilot in Italy which landed in Swiss land.I'm sorry for Ethiopia.

  • @NA-nq8lc
    @NA-nq8lc 4 роки тому

    ከባለስልጣናት ግድያ ጀርባ ሁሌም መንግሥት ነው ያለው:: ግልፅና ግልብ ነው::

  • @dagmayaweke4695
    @dagmayaweke4695 4 роки тому

    With the same good talking you should talk about Ermias Amelga too.

  • @tedaraya6365
    @tedaraya6365 4 роки тому

    Let him write. how can we follow him till now

  • @felekeshebeta3756
    @felekeshebeta3756 4 роки тому

    "50 ዓመት ይቺ ሀገር ተሰቃይታም የማያምኑ"

  • @lamrof
    @lamrof 4 роки тому

    አሁን ያ ጂንስ ያደረገው የለበሰው ሸሚዝ ሰው ፊት፣ የህዝብ መድረክ ላይ መቅረብ ያለበት ነው? ምነው ጃል እንዲህ ያለ ቅጡን ያጣ ዝንጉርጉር ብልጭልጭ ነገር አድርጎ መቅረብ። ወግ ያለው ሸሚዝ በ60ብር ገዝቻለሁ አዲሳባ፤ እኔ ያለሁበት አሜሪካ እንኳ ብርቅ የሆነ።

  • @BeteWoldeyohannes-sk2uo
    @BeteWoldeyohannes-sk2uo 4 місяці тому

    Guys.,. If you’re going to interview a guest refrain from interrupting !!! I lost interest in listening to this chitchat any further good bye!!

  • @Jah-yesteserial
    @Jah-yesteserial 4 роки тому

    በጣም ገራሚ እና ጠቃሚ ውይይት ነው' ዶክተር ኦርስዶ ነገሮች በጣም የገቡህና የምትሰጠው ማብራሪያ ሁሉ በጣም ነው የሚያስደስተኝ፣ ያረድም ጥሩ መረጃ እና አስተያየት ስለነገርከን እናመሰግናለን! በርቱ የውሸታም ፖለቲክስ ገና ይገለጣል!!!!

  • @0135827
    @0135827 4 роки тому

    I wish you guys can teach our politicians how to debate around the table with out firing a bullet or swinging a machete.

  • @meneziwmera2287
    @meneziwmera2287 4 роки тому

    ግን ደግሞ በቆየው ዘመን የበላይና የበታች ሚባል ክፍፍል እንደነበር ፤ በተለይ በአፍ መፍቻ ቋንቋ የመማር ፤ራስን በራስ የማስተዳዳር ችግር እንደነበር መካድ አይቻልም ….
    እጅግ ስለኢትዮጵያ የሚያቀነቅኑ ግን ደግሞ ስለሌላው ማንነት ባህል ቋንቋ ጉዳይ ግድ ያልነበረው አካልም ብዙ ነበር ፤

  • @E1472
    @E1472 4 роки тому +1

    It is too hard to follow your arguments when you guys are interrupting each other every few second.

  • @dan125874
    @dan125874 4 роки тому

    can you put the name of the polish writer and the book itself here please

  • @asfawgetachew713
    @asfawgetachew713 4 роки тому

    Thanks to The real dr. Ersado for your description of what ethnic poltics and the delusions of if in Ethiopian poltics the last 50 years especially the last 30 years and your best description of that ethnic and socity has no boundaries that big mistake of TPLF/EPRDF current federalism .

  • @berehaneghaile848
    @berehaneghaile848 4 роки тому

    ውይይቱ ጫጫታ ብዛ፤ ተደማመጡ።

  • @samsonkidane9334
    @samsonkidane9334 4 роки тому

    ዋለልኝ ማለት የዘመኑ ጀዋር ማለት ነው ሽብርተኛ የሰላም ፅር ነው።

  • @teklaygebremariam4168
    @teklaygebremariam4168 4 роки тому

    ኣቤት ብቃት ኣቤት እውቀት
    ዋለልኝ ኮርጆ እንኳን ፅሁፉን ቢያቀርበው ልደት አዳራሽ ውስጥ የነበሩት ተማሪዎች ኢትዮጵያዊያን አልነበሩም
    እናንተ ክፍ ዝቅ እንደምታደርጉት እነሱ ለምን አልሞገቱትም እነርሱ ከናንት ያንሰ ንቃት ነበራቸው
    ስላለውና ስለፃፈው ነገር እንድ ዘለላ ዓረፍተነገር discuss ሳታደርጉ ይህ ሁሉ ውግዘት የውጭ ሰዎች እንደምን ይህንን ፅሑፍ ሊያቀርቡ ይችላሉ
    ደደቦች

  • @dagemsolomon8797
    @dagemsolomon8797 4 роки тому

    anyone, please let me know the full name of yared , the journalist didn't introduce them

    • @1melkt
      @1melkt 4 роки тому

      Yared Haile Mesqel

  • @dessalegnbefekadu7371
    @dessalegnbefekadu7371 3 роки тому

    Richard Greenfield ???????

  • @ermiasnagash88
    @ermiasnagash88 4 роки тому +1

    Please read the history don't tell your assumption.

  • @tekestegebrehiwot1281
    @tekestegebrehiwot1281 4 роки тому

    motwal bilachu yefelegachuten awreu

  • @so2bk
    @so2bk Місяць тому

    Walelign Mekonin one of the best revolutionaries that saved nation nationalities from slavery.
    You guys are arrogant & out of touch.

  • @yetinayeteshete5220
    @yetinayeteshete5220 4 роки тому

    በጉጉት የምጠብቀው ውይይት ነው

  • @derejeshiferaw8334
    @derejeshiferaw8334 4 роки тому

    Dear Moderator had you had a chance to do your homework before this show you would have intervened and mentioned the autobiography book of Mr. Assefa Adefres's book ከ ባቹማ እስከ ቨርጂኒያ as he illustrated vividly the naive attempt of Walelign Mekonnen and his group hijacking Ethiopian Airlines. In the same book, the wonderful pilot Capitain Kesela (who safely land the aircraft from 40000 feet with two engines only) also mentioned on page 172. Dr. Arsido and Yared thank you for your ideas. We need this kind of discussion rather than sensational and/or fake news.

  • @user-yh9du3pd3k
    @user-yh9du3pd3k 6 місяців тому

    Logical discusion!

  • @Yoseph96
    @Yoseph96 4 роки тому +1

    STOP INTERRUPTING EACH OTHER. OOOOOOOOOOOOOO.

  • @samiya6526
    @samiya6526 4 роки тому +1

    ዋለልኝ መኮንን-አፈና ያልገታው የአመጽ ድምጽ
    ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
    -----
    ነገ ህዳር 29/2008 የብሄርና ብሄረሰቦች ቀን ሊከበር ነው፡፡ ይህ ቀን ለበዓሉ አከባበር የተመረጠው የኢፌዴሪ ህገ-መንግሥት የጸደቀበት ስለሆነ ነው ተብሏል፡፡ ታዲያ በዚሁ ቀን አንድ ታላቅ አብዮታዊ ተገድሎ ነበር፡፡ የሚገርመው ነገር በዚህ ዕለት የሞተው ሰውዬ በኢትዮጵያ ውስጥ የብሄርና ብሄረሰቦች መብት መከበር አለበት በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ የጻፈ ሰው መሆኑ ነው፡፡
    *****
    ህዳር 29/1964፡፡ ረፋዱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 708 ጄት አውሮፕላን ከአዲስ አበባ በአስመራ በኩል ወደ አቴንስ ሊበር ነው፡፡ በአውሮፕላኑ የሚጓዙ መንገደኞች ቦታ ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ ሰባት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ከአውሮፕላኑ ውስጥ ተሳፍረዋል፡፡ የበረራው ሰዓት ሲደርስ አውሮፕላኑ ከመሬት ተነሳ፡፡ ከሰማዩ ገብቶ መብረር ሲጀምር ግን ያልታሰበ ሁኔታ ተከሰተ፡፡ እነዚያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አውሮፕላኑን በቁጥጥራቸው ስር ማዋላቸውን አስታወቁ፡፡ እነርሱ ወደሚፈልጉት ሀገር እንዲበሩም አብራሪዎቹን አዘዟቸው፡፡ ተማሪዎቹ የጠለፋ እወጃውን ካሰሙ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ሌላ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ፡፡ አውሮፕላኑን ከጠለፋ እንዲታደጉ የታዘዙ ኮማንዶዎች በቀጥታ በጠላፊዎቹ ላይ በማነጣጠር ተኮሱባቸው፡፡ ስድስት ጠላፊዎች ተገደሉ፡፡ አንዲት ጓደኛቸው ደግሞ በከባድ ሁኔታ ቆሰለች፡፡ የአውሮፕላኑ ወለል በሙታኑ ደም ታጠበ፡፡
    *****
    በዚያች ዕለት የሞተው ታዋቂው የተማሪዎች ንቅናቄ መሪ ዋለልኝ መኮንን ነበር፡፡ ከርሱ ጋር የተገደሉትም ማርታ መብራህቱ፣ ጌታቸው ሀብቴ፣ ተስፋዬ ቢረጋ፣ ዮሐንስ በፈቃዱ እና አማኑኤል ዮሐንስ ናቸው፡፡ እነዚያ ወጣቶች አውሮፕላኑን ለመጥለፍ የሞከሩት የስርዓቱ ክትትል መፈናፈኛ ስላሳጣቸው ነው፡፡ ዓላማቸው ወደ ውጪ ከኮበለሉት ጓደኞቻቸው ጋር በመቀላቀል ለስር-ነቀል ለውጥ የሚታገል ድርጅት መመስረት ነበር፡፡ ከድርጅቱ ምስረታ በኋላም ወደ ሀገር ቤት ተመልሰው ትግሉን በየአቅጣጫው ለማፋፋም አስበዋል፡፡ ሆኖም እንደተመኙት አልሆነላቸውም፡፡ አውሮፕላን ለመጥለፍ ማቀዳቸው ቀደም ብሎ ተጠቁሞ ስለነበር የጸጥታው ክፍል በአየር ላይ አፍኖ አስቀራቸው፡፡
    *****
    ከላይ በተገለጸው አሳዛኝ ገቢር (ትራጄዲ) ህይወቱ የተቋጨው ዋለልኝ መኮንን በወሎ ክፍለ ሀገር የሳይንት (ቦረና) አውራጃ ተወላጅ ነው፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በደሴው ንጉሥ ሚካኤል ትምህርት ቤት አጠናቀቀ፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱንም እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ ደሴ ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ወይዘሮ ስሒን ት/ቤት ተከታተለ፡፡ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን ደግሞ የዘመኑ ምርጥ ተማሪዎች መማሪያ በነበረው በአዲስ አበባው በዕደማሪያም ትምህርት ቤት አገባደደ፡፡ በ1958 ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከገባ በኋላም እጅግ የተለየ አብዮታዊ ሆነ፡፡
    ዋለልኝ በ1959 በዩኒቨርሲቲው በተደረገው የግጥም ውድድር “ሙት ወቃሽህ መጣው” በሚለው ግጥም አንደኛ ወጥቷል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ህብረት ይዘጋጅ በነበረው የታገል መጽሔት ከማንም በላይ የነቃ ተሳትፎ ያደርግ ነበር፡፡ በህቡዕ የሚዘጋጁ ጽሑፎችንም እያዘጋጀ ያሰራጭም ነበር፡፡ በተለይ “አዞዎቹ” የሚባለው የስር-ነቀል ለውጥ ደጋፊ ተማሪዎች ስብስብ በአቋም ደረጃ የተስማማባቸውን ሀሳቦች በጽሑፍ እያቀናበረ የሚያዘጋጀው እርሱ እንደነበር በያኔው እንቅስቃሴ የተሳተፉትም ሆነ የዘመኑን ታሪክ ያጠኑ ምሁራን ይመሰክራሉ፡፡
    ከዋለልኝ ጽሑፎች መካከል ዝነኛ የሆኑት ሁለት ናቸው፡፡ አንደኛው ከላይ የጠቀስኩትና ህዳር 10/1961 በታተመው “ታገል መጽሔት” ላይ የወጣው “የብሄረሰቦች ጥያቄ በኢትዮጵያ” የሚል ርዕስ ያለው ጽሑፍ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በ1962 የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት የነበረው ጥላሁን ግዛው ሲገደል የአጼው ስርዓት በተማሪዎቹ ላይ ያደረገውን ዛቻ በመቃወም “ለአዋጁ አዋጅ” በሚል ርዕስ በህቡዕ ጽፎ የበተነው ጽሑፍ ነው፡፡ ዋለልኝ በጽሑፎቹ ሳቢያ በተደጋጋሚ ጊዜያት ታስሯል፡፡ በተለይ “ለአዋጁ አዋጅ”ን የጻፈው እርሱ መሆኑ ሲታወቅ በችሎት ፊት ቀርቦ አምስት ዓመት እስራት ተፈርዶበታል (ሆኖም ተማሪዎች ባደረጉት ከፍተኛ የተቃውሞ ጫና ከዓመት በኋላ ተፈትቷል)፡፡
    ከ1962 በኋላ ሁለት ክስተቶች የተማሪውን ንቅናቄ አቅጣጫ ቀይረውታል፡፡ እነዚህም በስርዓቱ የሚደረገው አፈና መጠናከር እና የድርጅት ምስረታ ጥያቄ መቀስቀስ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደ ቀድሞው ጊዜ የተቃውሞ ሰልፍ ከማድረግ ይልቅ የጥናት ክበቦችን እየመሰረቱ መወያየቱን መረጡ (የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በተቃውሞ ቀጠሉ)፡፡ ዋለልኝም በውይይት ክበቡ በሚያደርገው ጥናት ላይ አተኮረ፡፡ ከሀገር ተሰደው በአልጄሪያ ከሚገኙት እነ ብርሀነ መስቀል ረዳ ጋር በሚያደርገው የደብዳቤ ልውውጥ አማካኝነትም ሰፊ መሰረት ያለው ድርጅት ለመመስረት በሚደረገው ውይይትም ውስጥ ይሳተፍ ነበር፡፡ ህዳር 29/1964 በውጪ ካሉት ጓደኞቹ ጋር ለመቀላቀል ሲል አውሮፕላን ጠለፈ፡፡ ሆኖም ካሰበው ስፍራ ሳይደርስ በአውሮፕላኑ ውስጥ ተገደለ፡፡
    *****
    ከያኔው የተማሪዎች ንቅናቄ መሪዎች መካከል ዋለልኝ መኮንን ልዩ የሚያደርገው አንድ ነገር አለ፡፡ ይኸውም የተለያየ አመለካከት ባላቸው የፖለቲካ ድርጅቶች እንደ ታላቅ ሰማዕት የሚታይ መሆኑ ነው፡፡ ደርግ፣ ኢህአፓ፣ ህወሐት፣ ኦነግ፣ ሻዕቢያ፣ መኢሶን፣ ወዘተ… ሁሉም ለርሱ በጎ አመለካከት ነው ያላቸው፡፡ ታዲያ በዋለልኝ ታሪክ ላይ የሚደረገው ሽሚያም በጣም የጠነከረ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ታሪኩን ከራሳቸው ድርጅት ጋር ለማቆራኘት ይሞክራሉ፡፡ በወቅቱ የነበረው የርሱና የጓደኞቹ አሰላለፍ ሲገመገም ግን ዋለልኝ ኢህአፓን ከመሰረቱ ወጣቶች ጋር ተመሳሳይ የፖለቲካ መስመር የነበረው ሆኖ ነው የሚታየው፡፡ ኢህአፓን የመሰረቱትም የርሱ የቅርብ ጓደኞች ናቸው፡፡ በመሆኑም ዋለልኝ በህይወት ቢሰነብት ኖሮ የዚሁ ድርጅት አባል ይሆን ነበር ተብሎ ነው የሚገመተው፡፡
    *****
    ዋለልኝ መኮንን ከብዙ በጥቂቱ ይህ ነበር፡፡ ወደፊት ሰፋ ባለ ሁኔታ ስለርሱ እጽፋለሁ ብዬ አስባለሁ፡፡ እናንተም በበኩላችሁ የምታውቁትን እንድታጋሩን በአክብሮት እንጠይቃችኋለን፡፡
    ------
    ሰላም

  • @berehaneghaile848
    @berehaneghaile848 4 роки тому

    አስስታችሁን ስታችዃል የዋለልኝ ትችት መች አለቀ

  • @jobasfaw7458
    @jobasfaw7458 3 роки тому

    The guy doesn't listen at all.