DW Amharic የሐምሌ 14 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Поділитися
Вставка
  • Опубліковано 5 вер 2024
  • የሐምሌ 14 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜና
    በጦርነት እየታመሰች ባለችው የሱዳናዋ የፖርት ሱዳን ከተማ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ 9 ሰዎች መሞታቸውን የሃገሪቱ ፖሊስ አስታወቀ። በአንድ የመኖሪያ ሕንጻ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ በርካቶች መጎዳታቸውንም ፖሊስ አክሏል።
    የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ ከመንግስት ከመነጋገር በፊት ፍትህ ማረጋገጥ ይገባል አሉ። ኦዲንጋ ሕዝባዊ አመጽ አገሪቷን ሊያጠፋት ይችላል ሲሉም አስጠንቅቋል።
    እስራኤል በተለያዩ የጋዛ ሰርጥ አካባቢዎች በአለፉት 24 ሰዓታት በፈጸመችው ጥቃት 64 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የጋዛ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
    የዩክሬይን ፕሬዚደንት ቭሎደሚር ዘለንስኪ ወታደሮቻቸውንና ወታደራዊ ተቋሞቻቸውን ከሩስያ ጥቃት ለመከላከል ረዥም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳይሎች እንደሚያስፈልጋቸው ተናገሩ።
    ፕረዚደንቱ ይህን የተናገሩት ሩስያ በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ለአምስተኛ ጊዜ ግዙፍ የተባለለት የድሮንና የሚሳይል ጥቃት ዛሬ በክዬቭ ከተማ ላይ መፈጸሟን ተከትሎ ነው።
    ሁለት የአሜሪካ ስትራተጂክ ቦምብ ጣይ የጦር ጀቶች ሉአላዊ የአየር ግዛቷን ጥሰው መግባታቸውን ሩስያ አስታወቀች። ሩስያ ድንበሯን መጣሱን ተከትሎ የጦር ጀቶቿ ወደ አከባቢው ሲበሩ የአሜሪካ የጦር ጀቶች መሸሻቸውንም አክላለች።

КОМЕНТАРІ • 6

  • @AyshaRak
    @AyshaRak Місяць тому +1

    Yooyyaa

  • @sisayneberga3616
    @sisayneberga3616 Місяць тому

    በፍቅር ማደምጣችሁ ከእምድብር❤❤

  • @Alaelo-d3t
    @Alaelo-d3t Місяць тому +1

    ዶቸ ቬሌ ለትኩስ መረጃዎቻቹ በጉጉት የምጠባበቃቹ አድማጫቹና ደንበኛቹነኝ በርቱልኝ ጎኒ ጊና እባላለሁ ከቀቤና ልዩ ወረዳ ዋና ከተማ ወልቂጤ

  • @Alaelo-d3t
    @Alaelo-d3t Місяць тому

    ዶቸ ቬሌ ለትኩስ መረጃዎቻቹ በጉጉት የምጠባበቃቹ አድማጫቹና ደንበኛቹነኝ በርቱልኝ ጎኒ ጊና እባላለሁ ከቀቤና ልዩ ወረዳ ዋና ከተማ ወልቂጤ❤

  • @Alaelo-d3t
    @Alaelo-d3t Місяць тому

    ዶቸ ቬሌ ለትኩስ መረጃዎቻቹ በጉጉት የምጠባበቃቹ አድማጫቹና ደንበኛቹነኝ በርቱልኝ ጎኒ ጊና እባላለሁ ከቀቤና ልዩ ወረዳ ዋና ከተማ ወልቂጤ

  • @Alaelo-d3t
    @Alaelo-d3t Місяць тому

    ዶቸ ቬሌ ለትኩስ መረጃዎቻቹ በጉጉት የምጠባበቃቹ አድማጫቹና ደንበኛቹነኝ በርቱልኝ ጎኒ ጊና እባላለሁ ከቀቤና ልዩ ወረዳ ዋና ከተማ ወልቂጤ❤